በቴል አቪቭ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በኢራን ጥቃት መጠነኛ ጉዳት ደረሰበት

Date:

እሁድ ምሽት ኢራን ባስወነጨፈቻቸው ሚሳዔሎች በቴል አቪቭ በሚገኘው የኤምባሲያቸው ቅርንጫፍ “መጠነኛ ጉዳት” መድረሱን በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር አስታወቁ።

ማይክ ሃካቢ በኤክስ ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት ቆንስላው “በኢራን ሚሳዔሎች ንዝረት” ጉዳት ስለደሰበት ዝግ ሆኖ ይቆያል ብለዋል።

የአሜሪካ ኤምባሲ በቴል አቪቭ እና በኢየሩሳሌም የሚገኙ ሠራተኞቹ መጠለያ ውስጥ እንዲቆዩ በትናንትናው ዕለት አሳስቦ ነበር።

በሚሳዔል ጥቃቱ የተጎዳ የኤምባሲው ሠራተኛ እንደሌለም አምባሳደሩ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...