በትግራይ ክልል ኤች አይ ቪ ቫይረስ ከነበረበት ደረጃ ወደ 1.42 በመቶ ቀንሶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ የበሽታ ስርጭቱ 3 በመቶ መድረሱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡
ከጦርነቱ በኋላ በቅርቡ በተካሄደው ጥናት የ ስርጭቱ መጠን ሴተኛ አዳሪዎች ላይ 8.5 በመቶ እንዲሁም ተፈናቃዮች ላይ ወደ 5.5 በመቶ መሆኑን በትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የኤች አይ ቪ ኤድስ ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ ፍሰሀ ብርሀነ ተናግረዋል፡፡
ለስርጭቱ መጨመር በሰአቱ የነበረው የመድሀኒት አቅርቦት እጥረት እና የኮንዶም አቅርቦት አለመኖር በዋናነት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡
እንዲሁም ስለ ኤች አይ ቪ ያለው ግንዛቤ እጅግ አናሳ መሆኑ ሌላኛው ምክኒያት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
አሁን ላይ ግን አልፎ አልፎ መቆራረጦች ቢኖሩም የመድሀኒት አቅርቦት እጥረት አለመኖኑን ዳይሬክተሩ አንስተዋል፡፡
አሁን ላይ ኤች አይ ቪ ኤድስ አደጋ መሆኑን ህብረተሰቡ ሊገነዘብ እንደሚገባ እና እያንዳንዱ ግለሰብ ከቤቱ ጀምሮ ስለ በሽታው ማወቅ እንዳለበት የገለጹት ሃላፊው የሃይማኖት ተቁዋማትን ጨምሮ ስለበሽታው ግንዛቤ በመፍጠሩ በኩል ሁሉም አካል ሃላፊነቱን እንዲወጣ የሚል መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም
