በትግራይ ክልል የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት 3 በመቶ ደርሷል ተባለ

Date:

በትግራይ ክልል ኤች አይ ቪ ቫይረስ ከነበረበት ደረጃ ወደ 1.42 በመቶ ቀንሶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ የበሽታ ስርጭቱ 3 በመቶ መድረሱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

ከጦርነቱ በኋላ በቅርቡ በተካሄደው ጥናት የ ስርጭቱ መጠን ሴተኛ አዳሪዎች ላይ 8.5 በመቶ እንዲሁም ተፈናቃዮች ላይ ወደ 5.5 በመቶ መሆኑን በትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የኤች አይ ቪ ኤድስ ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ ፍሰሀ ብርሀነ ተናግረዋል፡፡

ለስርጭቱ መጨመር በሰአቱ የነበረው የመድሀኒት አቅርቦት እጥረት እና የኮንዶም አቅርቦት አለመኖር በዋናነት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡

እንዲሁም ስለ ኤች አይ ቪ ያለው ግንዛቤ እጅግ አናሳ መሆኑ ሌላኛው ምክኒያት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

አሁን ላይ ግን አልፎ አልፎ መቆራረጦች ቢኖሩም የመድሀኒት አቅርቦት እጥረት አለመኖኑን ዳይሬክተሩ አንስተዋል፡፡

አሁን ላይ ኤች አይ ቪ ኤድስ አደጋ መሆኑን ህብረተሰቡ ሊገነዘብ እንደሚገባ እና እያንዳንዱ ግለሰብ ከቤቱ ጀምሮ ስለ በሽታው ማወቅ እንዳለበት የገለጹት ሃላፊው የሃይማኖት ተቁዋማትን ጨምሮ ስለበሽታው ግንዛቤ በመፍጠሩ በኩል ሁሉም አካል ሃላፊነቱን እንዲወጣ የሚል መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...