ሽር -ጉድ ኮንሰርት የሚል ርዕስ የተሰጠው አንጋፋ እና ወጣት ድምፃዊያንን አጣምሯል፡፡ ይህ ኮንሰርት ሽር -ጉድ ኢንተርቴመንት አዘጋጅነት በአዲስ አበባ በሚልየም አዳራሽ ለማከናወን ዝግጅቱን ጨርሷል፡፡
በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፉ በጥምረት በዘመን ትውስታ ውስጥ የማይጠፉ የዘጠናዎቹ አድማቂዎች ከረዥም አመታት በኃላ በመድረክ ዳግም ይገናኛሉ፡፡ ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ እና አለማየሁ ሂርጶ(ኢቫንጋዲ) በተጨማሪ አንጋፋው ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ ተካቶበታል፡፡በዚህ ትውልድ በብዙ ዘንድ ተወዳጅነት ያተረፈችሁ ድምፃዊ ሜላት ቀለም ወርቅ ትገኝበታለች ተብሏል፡፡
ሽርጉድ ኮንሰርት ቅዳሜ ሚያዝያ 18/2017 በሚልየም አዳራሽ ይገናወናል፡፡ አዘጋጅ ሸርጉድ ኢንተርቴመንት፡፡ ቀኑ ሲደርስ እየተከታተልን የምንገልፅላችሁ ይሆናል
ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ
