Home ልዩ ልዩ ዜና በትግራይ ጉዳይ ኢዜማ መግለጫ አወጣ

በትግራይ ጉዳይ ኢዜማ መግለጫ አወጣ

በትግራይ ጉዳይ ኢዜማ መግለጫ አወጣ

ፌደራል መንግስቱ በትግራይ ክልል የሚታየውን ውጥረት በአስቸኳይ ሊያስቆም ይገባል፣ ዘላቂ መፍትሔም ያስፈልገዋል!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ከፕሪቶሪያው ሥምምነት መፈጸም በኋላ አንጻራዊ ሰላም እየታየበት የነበረው የትግራይ ክልል ሁኔታ የፌደራል መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ሥምምነት መሠረት ታጣቂ ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታት ኃላፊነቱን በአግባቡ ባለመወጣቱ፣ አካታች የሆነ ጊዜያዊ የሽግግር መንግስት አለመመስረቱን ተከትሎ ህወሓት የእርስ በእርስ ፍትጊያ ውስጥ ገብቶ በትግራይ ክልል ውጥረት መንገሱን ይገነዘባል፡፡ በእርግጥ ይህ ሁኔታ እንዳይፈጠር በመስጋት የፕሪቶሪያ ስምምነት በአግባቡ ተተግብሮ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ደጋግመን ያቀረብነውን ማሳሰቢያ ሳይሰማ በዝምታ ያለፈው ፌደራል መንግስቱ አሁን ለተፈጠረው ቀውስ ድርሻውን መውሰድ እንዳለበት ሊያውቅ ይገባል፡፡

ኢዜማ በፓርቲው የውስጥ ጉዳይ ላይ የትኛውንም አስተያየት የመስጠት ፍላጎቱ የለውም፡፡ ሆኖም በህወሓት ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ የስልጣን ሽኩቻ ተከትሎ በክልሉ ያሉ የታጠቁ ኃይሎች እየሄዱበት ያለው ግትር፣ ግጭት ቀስቃሽ ህገወጥ እንቅስቃሴ ግን በጠቅላላው እንደሀገር በተለይ ደግሞ በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ ንፁሀን ዜጎች ላይ የሚያመጣውን ምጣኔ ኃብታዊ፣ ማኀበራዊ ብሎም የሰላምና የደኀንነት አስከፊ አደጋ በቅጡ እንረዳለን፣ ያሳስበናልም፡፡