በትግራይ ጉዳይ ኢዜማ መግለጫ አወጣ

Date:

ፌደራል መንግስቱ በትግራይ ክልል የሚታየውን ውጥረት በአስቸኳይ ሊያስቆም ይገባል፣ ዘላቂ መፍትሔም ያስፈልገዋል!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ከፕሪቶሪያው ሥምምነት መፈጸም በኋላ አንጻራዊ ሰላም እየታየበት የነበረው የትግራይ ክልል ሁኔታ የፌደራል መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ሥምምነት መሠረት ታጣቂ ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታት ኃላፊነቱን በአግባቡ ባለመወጣቱ፣ አካታች የሆነ ጊዜያዊ የሽግግር መንግስት አለመመስረቱን ተከትሎ ህወሓት የእርስ በእርስ ፍትጊያ ውስጥ ገብቶ በትግራይ ክልል ውጥረት መንገሱን ይገነዘባል፡፡ በእርግጥ ይህ ሁኔታ እንዳይፈጠር በመስጋት የፕሪቶሪያ ስምምነት በአግባቡ ተተግብሮ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ደጋግመን ያቀረብነውን ማሳሰቢያ ሳይሰማ በዝምታ ያለፈው ፌደራል መንግስቱ አሁን ለተፈጠረው ቀውስ ድርሻውን መውሰድ እንዳለበት ሊያውቅ ይገባል፡፡

ኢዜማ በፓርቲው የውስጥ ጉዳይ ላይ የትኛውንም አስተያየት የመስጠት ፍላጎቱ የለውም፡፡ ሆኖም በህወሓት ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ የስልጣን ሽኩቻ ተከትሎ በክልሉ ያሉ የታጠቁ ኃይሎች እየሄዱበት ያለው ግትር፣ ግጭት ቀስቃሽ ህገወጥ እንቅስቃሴ ግን በጠቅላላው እንደሀገር በተለይ ደግሞ በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ ንፁሀን ዜጎች ላይ የሚያመጣውን ምጣኔ ኃብታዊ፣ ማኀበራዊ ብሎም የሰላምና የደኀንነት አስከፊ አደጋ በቅጡ እንረዳለን፣ ያሳስበናልም፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብር እና የደቡብ ሱዳን ፓውንድ በዓለም ላይ ደካማ አፈጻጸም ካሳዩት ተርታ ተመደቡ

 የኢትዮጵያ ብር እና የደቡብ ሱዳን ፓውንድ እ.ኤ.አ በ2025 (ከታኅሣሥ...

የኢራን ጠቅላይ መሪ የደረሰባቸው ከፍተኛ እና አካል የሚያጎድል ጉዳት እንደሆነ ተዘገበ

የኢራን ጠቅላይ መሪነት ሥልጣንን ከተረከቡ ወዲህ በአካል ያልታዩት ሞጅታባ...

ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የባህር ላይ የንግድ ጥምረት ለመመስረት ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የንግድ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ጅቡቲን የሚያካትት ባለሦስትዮሽ...

56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መሸጫ ተመሰገነ

ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር...