በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ 24 ሰዎች ሕይወት አለፈ

Date:

በአሜሪካ፣ ቴክሳስ ግዛት አርብ ዕለት ባጋጠመ የጎርፍ አደጋ ቢያንስ 24 ሰዎች ሲሞቱ በካምፕ ውስጥ የነበሩ ወደ 25 የሚጠጉ ሴት ታዳጊዎች መጥፋታቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ።

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በነጻነት ቀን ያጋጠመውን ይህንን የጎርፍ አደጋ “አስደንጋጭ” እና “አስከፊ ” ብለውታል።

የፌደራል ባለሥልጣናትም እርዳታ እያደረጉ እንደሆነ የቴክሳስ ገዥ ግሬግ አቦት ተናግረዋል።

ምንም እንኳን የግዛቷ ባለሥልጣናት በጎርፉ ምክንያት የገቡበት ያልታወቁ ሰዎችን ቁጥር ባያረጋግጡም ፍለጋው እና የነፍስ አድን ጥረቱ ሌሊቱን መቀጠሉን የግዛቷ ገዥ ገልጸዋል።

የጎርፍ አደጋው መንስዔ ግዛቷ በበርካታ ወራት የምታገኘው የዝናብ መጠን በጥቂት ሰዓታት ውስጥ መዝነቡ እንደሆነ ተገልጿል።

ጎርፉ ድልድዮችን ጠራርጎ ሲወስድ እና በከፍተኛ ፍጥነት የሚጓዝ ጎርፍ መንገዶችን ሲያጥለቀልቅ በማኅበራዊ ሚዲያ የተጋሩ ምስሎች አሳይተዋል።

የቴክሳስ ምክትል አስተዳዳሪ ዳን ፓትሪክ “ጎርፉ ከመከሰቱ በፊት የወንዙ የውሃ ከፍታ ጨምሮ ነበር።

በ45 ደቂቃ ውስጥ፣ ጉዳሉፕ ወንዝ 26 ጫማ ከፍታ ጨምሮ ነበር። አውዳሚ ጎርፍ ነው፤ ሕይወትን እና ንብረትን አጥፍቷል።” ብለዋል።

ፓትሪክ ጨምረውም ” ሕጻናቱ የገቡበት አልታወቀም ማለት ሞተዋል ማለት አይደለም፤ ከግንኙነት መስመር ወጥተው ሊሆን ይችላል” ሲሉ ቤተሰቦችን አጽናንተዋል።

bbc_amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...