በኢትዮጲያ ግዙፍ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል ተመረቀ

Date:

የኢትዮጲያ አየር መንገድ እጅግ ዘመናዊ የአውሮፕላን ጥገና ወርክሾፕን ጨምሮ ፥ ዘመናዊ መጋዘንን አስመርቋል።

አየር መንገዱ ይህንን ዘመናዊ ልዩ ልዩ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከላት የተካተቱበትን ግዙፍ ማእከል ከ 150 ሚሊየን ዶላር  በላይ በማውጣት  ማስገንባቱን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በምረቃው ወቅት ተናግረዋል።

በ150 ሚሊየን ዶላር ወጪ የተደረገባቸው  ፕሮጀክቶች የአውሮፕላን ክፍሎች መጠገኛ፣ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል እና ከሰው ንከኪ ነፃ የሆነ መጋዘን  ናቸው።

የጥገና ቁሳቁሶች የሚከማቹበት መጋዘኑ  በ15 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ መሆኑ ተገልፃል።

የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ፣ እና ሌሎች  የተቋሙ እና የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ፣ዲፕሎማቶች እንዲሁም በፕሮጀክቱ የተሳተፍ አካላት በምረቃው ወቅት ተገኝተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...