በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ የወባ መከላከያ ክትባት መሰጠት ተጀመረ

Date:

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው አዲስ የወባ መከላከያ ክትባት፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ቱርሚ ከተማ መተግበሩን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል::

ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ የሚሰጠው አዲሱ የወባ መከላከያ ክትባት፣ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚሰጥ መሆኑን የገለፁት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፤ ክትባቱ ውጤታማ ስለመሆኑ በጥናት መረጋገጡን ዘመቻውን ባስጀመሩበት ወቅት ተናግረዋል።

ዶ/ር ደረጀ አክለውም፤ አዲሱ የወባ መከላከያ ክትባት ከመደበኛ የክትባት ፕሮግራም ጋር ተቀናጅቶ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ58 ወረዳዎች መሰጠት እንደሚጀመር ገልፀዉ፤ ህብረተሰቡ ሌሎች የመከላከያ ዘዴዎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

አዲሱ የወባ መከላከያ ክትባት በክልሉ ህዝብ በተለይም ከ5 ዓመት በታች በሆኑ ህፃናት የሚደርሰውን ህመምና ሞት ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡

የወባ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ በዓይነቱ ለየት ያለ አዲስ የመኝታ አጎበር ስርጭት የተጀመረ ሲሆን፤ 3.5 ሚሊዮን አዲስ የመኝታ አጎበር ቅድሚያ ለሚሰጣቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሰራጭ ይሆናል ተብሏል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...