አዲስ ቪዥን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ በኢትዮጵያ ትልቁን “አዲስ ቪዥን” የተሰኘ ሁሉን አቀፍ የትምህርት ኤክስፖ 2025 ማዘጋጀቱን ገለጸ።
ኤክስፖው፤ ትምህርት ቤቶችንና ተማሪዎችን በሚያገለግሉ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የትምሀርት ተቋማትን፣ አቅራቢዎችን፣ አምራቾችንና አገልግሎት ሰጪዎችን አንድ ላይ በአንድ ቦታ እንደሚያገናኝ ዛሬ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተነግሯል።
ተሳታፊዎች ከብዙ ባለድርሻ አካላት ጋር ለመገናኘት፣ አዳዲስ ምርቶችንና ቴክኖሎጂዎችን ለመተዋወቅ እንዲሁም አዳዲስ ትምህርታዊ መፍትሄዎችን በአንድ ማእከላዊ ቦታ የማግኘት እድል ይኖራቸዋል ተብሏል።
በዚህ የትምህርት ኤክስፖ የትምሀርት ተቋማት፣ የትምህርት ቁሳቁሶችን፣ ዩኒፎርሞችን፣ አልባሳትን፣ መጫወቻዎችንና የመጫወቻ ሜዳ አቅራቢዎች ምርታቸዉንና አገልግሎታቸዉን ያስተዋውቃሉ።
በሥርዓተ ትምህርት ልማት፣ በትምህርት ፈጠራና በሙያ መመሪያ ላይ የፓነል ውይይቶች ይደረጋል እንዲሁም ተማሪዎች፣ ወላጆችና አስተማሪዎች የሚያወያዩባቸው መድረኮች ይካሄዳሉ።
ኤክስፖው ከነሃሴ 22-24 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ፣ ግዮን ሆቴል ይካሄዳል።
