በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

Date:

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ሲ ቫይረስ ጋር እንደሚኖሩ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በተቋሙ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ፍቃዱ የዴታ እንደገለጹት፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባካሄደው ጥናት የሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ አጠቃላይ ብሔራዊ የስርጭት መጠን ከ5.7 እስከ 6.9 በመቶ አካባቢ መሆኑ ተረጋግጧል።

ይህ ስርጭት መካከለኛ እና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ በመሆኑ፣ ሀገሪቱ በዓለም የጤና ድርጅት መሥፈርት መሠረት ቫይረሱ በስፋት ከሚታይባቸው ቀጠናዎች ተርታ እንድትገኝ አድርጓታል።

ለ16ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሄፓታይተስ ቀን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ማከናወኑን ዶክተር ፍቃዱ አንስተዋል።

በሽታው መጀመሪያ ላይ ምንም ዓይነት ምልክት ሳያሳይ የሚቆይ ዝምተኛ ገዳይ በመሆኑ፣ ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያስተላልፉ አድርጓቸዋል ብለዋል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በሽታውን በ2030 ከወረርሽኝ ደረጃ ለማውረድ እየሠራ መሆኑን ገልጸው፣ አዲስ የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር 90 በመቶ ለመቀነስ ማቀዱን ተናግረዋል።

ለአሐዱ ሬዲዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...