በኢትዮጵያ የመነጽር ጥራት ቁጥጥር እጦት ለከፋ የዓይን ችግር እያጋለጠ ነው

Date:

በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ ደረጃ የመነጽርን ጥራት እና ደረጃ የሚቆጣጠር አካል አለመኖሩን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አስታውቋል ። በዚህም የተነሳ ዜጎች ጥራቱ የተረጋገጠ መነጽር ስለማያገኙ ለከፋ የዓይን ጤና ህመም እየተጋለጡ መሆኑን ተጠቁሟል።

የኮሌጁ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ሳዲቅ ታጁ እንደተናገሩት፣ መነጽር በዓይን ጤና ውስጥ እንደ መድሃኒት የሚያገለግል የህክምና ቁስ ቢሆንም፣ ጥራቱንና ደረጃውን የሚለይለት እና የሚቆጣጠርለት አካል በሀገር አቀፍ ደረጃ የለም።

በዚህም ምክንያት ዜጎች ጥራቱ ያልተረጋገጠ ምርት በመግዛት ለተደጋጋሚ ወጪ እና ተጨማሪ የዓይን ችግር እየተጋለጡ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

በተጨማሪም የመነጽር ጥራት ቁጥጥር ባለመኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የመነጽር ቤቶች እና በየመንገዱ መነጽር የሚያዞሩ ግለሰቦች በመብዛታቸው፣ እንዳሻቸው ሰርተውና ዋጋ ተምነው ለተጠቃሚው እያቀረቡ ነው ብለዋል። ይህ ደግሞ ብዙዎችን ለከፋ የዓይን ጤና ችግር እያጋለጠ ነዉ ሲል ኢፕድ ባለሞያውን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል ።

መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆግ መነጽር እንዴት መሰራቱና መገጣጠም እንዳለበት፣ የት ቦታ መሰራቱ እንዳለበት፣ በምን ያህል የጥራት ደረጃ መሰራቱ እንዳለበት፣ በምን አይነት መልኩ መሸጥ እንዳለበት የሚሉትን ጉዳዮች ለይቶ የሚሰራ አካል መመደብና አፈጻጸሙን መቆጣጠር ያስፈልጋል ተብሏል።

Source: capitalethiopia

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...