በኢትዮጵያ 3.8 ሚልየን ዓመታት እድሜን ያስቆጠረ የራስ ቅል መገኘቱ ተገለፀ

Date:

በኢትዮጵያ 3.8 ሚልየን ዓመታት ዕድሜን ያስቆጠረ የኦስትራሎፒቴከስ አናሜንሲስ ዝርያ የኾነ የራስ ቅል መገኘቱ ተገለፀ። በአፋር ክልል ሚሌ አካባቢ መገኘቱ የተገለፀው ቅሪት አካል በዓለም አቀፍ አንትሮፖሎጂስቶች ቡድን የካቲት 2008 ዓ.ም. እንደተገኘ ማወቅ ተችሏል። የተገኘው የራስ ቅል ከዘመናዊ የሰው ልጅ ጋር ተዛማጅነት ካላቸው ቀደምት የኦስትራሎፒተከስ ዝርያዎች አንዱ የሆነው የኦስትራሎፒቲከስ አናሜንሲስ እንደኾነም ተነግሯል። ኦስትራሎፒቲከስ አናሜንሲስ ከዚህ ቀደም የሚታወቀው በመንጋጋ አጥንቶች፣ በተቆራረጡ ጥርሶች እና ጥቂት በተሰበሩ የእጅ አጥንቶች ሲኾን ይህ በተመራማሪዎቹ የተገኘው የራስ ቅል ሙሉ በመኾኑ የአውስትሮሎፒቲከስ አናሜንሲስ ዝርያ ምን እንደሚመስል ለማወቅ እንደሚረዳቸው እምነት ተጥሎበታል። የአውስትራሎፒትከስ አፋርነሲስ ዝርያ የኾነችው ሊሲ (ድንቅነሽ) በአፋር ክልል ሃዳር አካባቢ በፈረንጆች 1974 እንደተገኘች ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...