በዱባይ ወንጀል ፈጽመው በኢትዮጵያ ተደብቀዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች!!

Date:

በዱባይ ወንጀል ሠርተው በኢትዮጵያ የተሸሸጉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር በማዋል ምርመራ እየተካሄደ  መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል አስታወቁ።

ኮሚሽነሩ ይህንን ያስታወቁት፤ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የዱባይ ፖሊስ የምርመራ ቡድን ጋር በወንጀል ምርመራ ዙሪያ በተወያዩበት ወቅት ነው።

በዱባይ ወንጀል ሠርተው በኢትዮጵያ ተሸሸገው የነበሩና በቁጥጥር ስር ውለው ምርምራ እየተካሄደባቸው ናቸው የተባሉት ተጠርጣሪዎችን ብዛትም ሆነ የወንጀል አይነት በተመለከተ ፌደራል ፖሊስ የገለጸው  ነገር የለም።

በቀጣይ በሁለቱም ሀገራት ተፈላጊ የሆኑ ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ በመስጠት በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ በሚቻልበት ሁኔታም ላይ  መወያየታቸውን ከፌደራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን...

‹‹ሃገረ ትግራይ›› በዘመናት መነፅር ሲታይ

(አጭርዳሰሳ) በወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) የመጽሐፉርዕስ፡- ሃገረ ትግራይ የመጽሐፉ ዓይነት፡-...

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...