በጊኒ በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዙት የመማዲ ዱምቡያ ወታደራዊ መንግሥት፣ በሌሊት ባወጣው አዲስ አዋጅ ሦስት ዋና ዋና ተቃዋሚዎችን ጨምሮ 40 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማፍረሱን አስታወቀ።
የግዛት አስተዳደር ሚኒስቴር ውሳኔውን ያስተላለፈው ፓርቲዎቹ “ግዴታቸውን አልተወጡም” በሚል ምክንያት ሲሆን፣ አዋጁ የፓርቲዎቹን ምልክቶች መጠቀም የሚከለክልና ንብረቶቻቸውንም በቁጥጥር ሥር የሚያውል ነው።
ከፈረሱት መካከል በስደት የሚገኙት የሴሉ ዳሌይን ዲያሎ (UFDG) እና የቀድሞው ፕሬዝዳንት አልፋ ኮንዴ (RPG) ፓርቲዎች ይገኙበታል።
እ.ኤ.አ. ከ2021 ጀምሮ አገሪቱን በጠንካራ እጅ እየመሩ ያሉት ዱምቡያ፣ ተቃውሞዎችን በማገድና መሪዎችን በማሰር እንዲሁም በማሳደድ ይወቀሳሉ።
የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪል ማኅበራት ድርጊቱን “አምባገነናዊ” በማለት የኮነኑት ሲሆን፣ እንደ ዑመር ሲላ እና ማማዱ ቢሎ ባህ ያሉ ታዋቂ አክቲቪስቶች ከሐምሌ 2024 ጀምሮ በግዳጅ መሰወራቸው በጊኒ ያለውን የሰብአዊ መብት ረገጣ ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
ይህ እርምጃ በሀገሪቱ ያለውን የዴሞክራሲ ተስፋ ይበልጥ ያጨለመ እንደሆነ ተነግሯል።
