በጋምቤላ ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከሰተ

Date:

በጋምቤላ ከተማ ሌሊቱን በጣለው ከባድ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል ። በተለይ በ05 ቀበሌ አንዳንድ አካባቢ የግለሰቦች መኖሪያ ቤት ውስጥ በመግባት በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን የእግረኛ እና የመኪና መንገዶች ላይም ውሃ ስለተኛባቸው ለመተላለፍ አስቸጋሪ አድርጎታል ።

የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ሳይመን ሙን ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ከክረምት ዝናብ ጋር ተያይዞ በሰውና ንብረት ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል ።

የጎርፍ መፋሰሻ ቱቦዎችን በመክፈት የውሃ ፍሰትን መቆጣጠር እንደሚገባ ገልጸዋል ።

የክረምት ወራት ገና ከመሆኑ የተነሳ የዝናብ መጠን ሊጨምር ስለሚችል የከተማችን ነዋሪዎች ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባቸው ጨምረው ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...