በጣቷ የምትስለው አርቲስት የአውስትራሊያን የሥነ ጥበብ ሽልማት አሸነፈ

Date:

የፊሊፒን -አውስትራሊያ ዜግነት ያላት አርቲስት ሎሪቤል ስፒሮቭስኪ የአርኪባልድ ሽልማት ያገኘች ሲሆብ የአውስትራሊያ እጅግ የተከበረ የጥበብ ሽልማትን ተቀዳጅታለች።

የአሸናፊነት ስራዋ የአቦርጂናል አውስትራሊያዊ ሙዚቀኛ ዊልያም ባርተን ምስል ሲሆን በጣቶቿ የቀባችው ይህው ስራ የነርቭ ጉዳት ያለባት መሆኑ የሥዕል ስራዋን ከባድ አድርጎታል።

ለብዙ ጊዜ የአርኪባልድ ሽልማት የመጨረሻ እጩ የነበረችው ወይዘሮ ስፒሮቭስኪ ህዝቡ ስራዋን ወዶ በመምረጡ “በጣም ተደስቻለሁ” ብላለች።

በኒው ሳውዝ ዌልስ የስነ ጥበብ ጋለሪ በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገረችው “እነዚህ አመታት አስቸጋሪ ነበሩ እናም ይህ አጠቃላይ ልምድ እንዳገኝ እና በስተመጨረሻን ቆንጆ እፎይታ እና ሽልማት ነው” ብላለች

ዊልያም እርሱን እንድስለው ስለፈቀደልኝ እና ለሥራዬ በሚሰጠኝ አስተያየት በጣም ትሑት ስለሆነ ያለማቋረጥ አመስጋኝ ነኝ ብላለች። ወይዘሮ ስፒሮቭስኪ ለመጀመሪያ ጊዜ ሚስተር ባርተንን ባለፈው ኦክቶበር ሲያገኛት ከነርቭ ጉዳት በማገገም ላይ የነበረች ሲሆን የመሳል ችሎታዋ ተዳክሞ ነበር።

የቁም ሥዕሉ ሲሰራ የሚስተር ባርተንን ሙዚቃ ትጫወት ነበር። “ሙዚቃው ሲጀመር እጄ አነሳና ብሩሹን ወደ ጎን አስቀምጬ ጣቴን ለስላሳ ቀለም ውስጥ እነክር ነበር” ብላለች።

#ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...