ብሔራዊ ባንክ የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለገበያ ሊያቀርብ ነዉ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶችን (T-bills) በዘመናዊ መልኩ ወደ ገበያ የሚያቀርብበትን ስርዓት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ይህ አዲስ ስርዓት ዜጎች እና ኢንቨስተሮች በመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች ላይ ኢንቨስት በማድረግ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

የማዕከላዊ ባንኩ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ እንደገለጹት፣ ይህ ስርዓት የግምጃ ቤት ሰነዶችን ግብይት የበለጠ ግልጽ፣ ቀልጣፋ እና ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም፣ የቁጠባ ባህልን ለማበረታታት እና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ማለታቸውን ካፒታል ሰምቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፉን በማዘመን የግምጃ ቤት ሰነድ ገበያን ጨምሮ ወደ ወለድ ተመን ሥርዓት በመሸጋገር፣ ክፍት የገበያ ሥራዎችን በማስተዋወቅ እና በርካታ ፖሊሲዎችን በማስተካከል ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

እነዚህ ማሻሻያዎች የሀገሪቱን የፋይናንስ ስርዓት ለማጠናከር እና ለኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ ለማድረግ ያለሙ ናቸው።

እኤአ በ2019 ፍላጎት ያላቸው የፋይናንስ ተቋማት የግምጃ ቤት ሰነዶችን በጨረታ መግዛት እንዲችሉ መፈቀዱ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን የሚመጣው ለውጥ ዜጎች በቀጥታ እንዲሳተፉ ያስችላል።

ይህ ለዜጎች እና ለኢንቨስተሮች አዲስ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመፍጠር የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...