ብሔራዊ ባንክ የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለገበያ ሊያቀርብ ነዉ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶችን (T-bills) በዘመናዊ መልኩ ወደ ገበያ የሚያቀርብበትን ስርዓት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ይህ አዲስ ስርዓት ዜጎች እና ኢንቨስተሮች በመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች ላይ ኢንቨስት በማድረግ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

የማዕከላዊ ባንኩ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ እንደገለጹት፣ ይህ ስርዓት የግምጃ ቤት ሰነዶችን ግብይት የበለጠ ግልጽ፣ ቀልጣፋ እና ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም፣ የቁጠባ ባህልን ለማበረታታት እና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ማለታቸውን ካፒታል ሰምቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፉን በማዘመን የግምጃ ቤት ሰነድ ገበያን ጨምሮ ወደ ወለድ ተመን ሥርዓት በመሸጋገር፣ ክፍት የገበያ ሥራዎችን በማስተዋወቅ እና በርካታ ፖሊሲዎችን በማስተካከል ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

እነዚህ ማሻሻያዎች የሀገሪቱን የፋይናንስ ስርዓት ለማጠናከር እና ለኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ ለማድረግ ያለሙ ናቸው።

እኤአ በ2019 ፍላጎት ያላቸው የፋይናንስ ተቋማት የግምጃ ቤት ሰነዶችን በጨረታ መግዛት እንዲችሉ መፈቀዱ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን የሚመጣው ለውጥ ዜጎች በቀጥታ እንዲሳተፉ ያስችላል።

ይህ ለዜጎች እና ለኢንቨስተሮች አዲስ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመፍጠር የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...