ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

Date:

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ የእስር ማዘዣ አወጣች።

ወደ ጋዛ ሰብአዊ እርዳታ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ መርከብ በእስራኤል በቁጥጥር ሥር ከመዋሉ ጋር በተያያዘ በሚደረግ ምርመራ ምክንያት የእስር ማዘዣው እንደወጣ ተገልጿል።

የቱርክ የፍትሕ ሚኒስትር አኪን ጉርሌክ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ መውጣቱን በኤክስ ገጻቸው አስታውቀዋል።

ከአራት ወራት በፊት ከ40 አገራት የተውጣጡ ከ430 በላይ የፍልስጤም የመብት ተሟጋቾች በእስራኤል ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል።

የመብት ተሟጋቾቹ በመርከብ ወደ ጋዛ ሰብአዊ እርዳታ ይዘው እየተጓዙ ነበር።

ጋዛ ላይ የተጣለውን ዕቀባ የሚቃወም ንቅናቄ አባል የሆኑት የመብት ተሟጋቾቹ በቱርክ አውሮፕላኖች ከእስራኤል ወደ ቱርክ ተወስደዋል።

ቱርክ ከዚህ ቀደምም በኔታንያሁ እና ሌሎችም ባለሥልጣናት ላይ የእስር ማዘዣ አውጥታለች።

ይህም እስራኤል በጋዛ ከምትፈጽመው ድርጊት ጋር በተያያዘ “በዘር ጭፍጨፋ” ክሶች ምክንያት የወጣ የእስር ማዘዣ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...

«ግብጽ ዛቻውን አቁማ ወደ ድርድር ትግባ!»

ታዋቂው የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ዴቪድ ማትሳንጋ ግብጽ በኢትዮጵያ...

በብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ710 ሚሊዮን ዶላር በላይ ፍላጎት የቀረበበት መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የ500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ...