ማንችስተር ዩናይትድን በይፋ የተቀላቀለው ብራይን ምቤሞ የመልሶ ማጥቃት አጨዋወትን የሚወድ ተጫዋች ነው።
ምቤሞ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን ለብሬንትፎርድ በሁሉም የሊግ ጨዋታዎች ( 38 ጨዋታዎች ) ተሰልፎ ተጫውቶ ሀያ ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።
ምቤሞ በፊት መስመር በተለያዩ ቦታዎች ላይ ሲጫወት ምርጥ ብቃቱን ማሳየት የቻለው ከቀኝ መስመር እየተነሳ ሲጫወት ነው።
ምቤሞ የፍፁንም ቅጣት ምት እድሎችን በመጠቀም ረገድ ጥሩ ሲሆን ካገኛቸው አስራ ሁለት እድሎች አስራ አንዱን ከመረብ አሳርፏል።
ምቤሞ በተለይም ከጉዳት ነፃ ከሚባሉ ተጫዋቾች መካከል አንዱ መሆኑ ዩናይትድን ተጠቃሚ ያደርገዋል።
ተጫዋቹ ለመጨረሻ ጊዜ በጉዳት ከሜዳ የራቀው በ 2023/24 የውድድር ዘመን በቁርጭምጭሚት ጉዳት ቀዶ ጥገና ተደርጎለት ለሶስት ወራት ርቆ ነበር።
ምቤሞ ባለፉት አራት የውድድር ዓመታት መጫወት ያልቻለው በአስራ ስድስት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ነው።
ምቤም በ 2022 የአለም ዋንጫ ለካሜሩን ከመጫወቱ በፊት በእድሜ ቡድኖች ለፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫውቶ አሳልፏል።
@tikvahethsport
