Home ልዩ ልዩ ዜና ቦክሰኛው ግጥሚያ ላይ ህይወቱ አለፈ

ቦክሰኛው ግጥሚያ ላይ ህይወቱ አለፈ

የ40 ዓመቱ ናይጄሪያዊ ቡጢኛገብርኤል ኦላንሬዋጁ በቦክስ ግጥሚያ መኻል ህይወቱ አለፈ

ቡጢኛው አክራ ውስጥ ከጋናዊው ጆን ምባኑጉ ጋር የቀላል ሚዛን ፍልሚያ እያደረገ በነበረበት ወቅት በ3ኛው ዙር ራሱን ስቶ እንደወደቀ ተዘግቧል። የድንገተኛ ህክምና ቢደረግለትም ከ30 ደቂቃ በኋላ በጋናው ኮርሌ ቡ ሆስፒታል ህይወቱ ማለፉን የጋና ቦክስ ባለስልጣን አስታውቋል።

🥊 የኦላንሬዋጁ ሪከርዶች፦
• በድምሩ 23 ፍልሚያዎች
• 13 ድሎች (12ቱን በዝረራ)
• 8 ሽንፈቶች
• 2 አቻ

@sputnik_ethiopia