ቴሌ ብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017

Date:

«ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017» በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከመጋቢት 19 ቀን እስከ ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን በዛሬው እለት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጸው፥ ይህ ኤክስፖ ከዚህ ቀደም ከተደረጉ የንግድ ትርኢቶች የተለየ እና ልዩ የሚያደርጉት በርካታ ዝግጅቶች ማቀዱን ገልጿል።

በዚህ ኤክስፖ ጎብኚዎች የተለያዩ የፆም ምግቦች (በብፌ መልክ) በአንድ ቦታ በ150 ብር ከነፃ የስንቅ ማልት ጋር ያገኛሉ።

ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ የሆነውን የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በኤክስፖ ላይ በልዩ ሁኔታ ይተዋወቃል።

2.8 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የኤሌክትሪክ መኪና እና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል እንዲሁም አይቴል የሞባይል ቀፎ ለሽልማት ቀርቧል።

ከመደበኛው የንግድ ትርኢት ባለፈ የባህል፣ የትምህርት እና የመዝናኛ መድረክ የቀረበ ሲሆን የሀገራችንን ባህል እና እሴቶች የሚያንጸባርቁ ልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች ይኖሩታል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን እና ከሊያን ቢዝነስ ግሩኘ ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል፡፡ ሀገሬ ቴቪ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...