ቴሌ ብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017

Date:

«ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017» በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከመጋቢት 19 ቀን እስከ ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን በዛሬው እለት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጸው፥ ይህ ኤክስፖ ከዚህ ቀደም ከተደረጉ የንግድ ትርኢቶች የተለየ እና ልዩ የሚያደርጉት በርካታ ዝግጅቶች ማቀዱን ገልጿል።

በዚህ ኤክስፖ ጎብኚዎች የተለያዩ የፆም ምግቦች (በብፌ መልክ) በአንድ ቦታ በ150 ብር ከነፃ የስንቅ ማልት ጋር ያገኛሉ።

ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ የሆነውን የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በኤክስፖ ላይ በልዩ ሁኔታ ይተዋወቃል።

2.8 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የኤሌክትሪክ መኪና እና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል እንዲሁም አይቴል የሞባይል ቀፎ ለሽልማት ቀርቧል።

ከመደበኛው የንግድ ትርኢት ባለፈ የባህል፣ የትምህርት እና የመዝናኛ መድረክ የቀረበ ሲሆን የሀገራችንን ባህል እና እሴቶች የሚያንጸባርቁ ልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች ይኖሩታል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን እና ከሊያን ቢዝነስ ግሩኘ ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል፡፡ ሀገሬ ቴቪ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...

ሕወሓት ድብረጺዮንን የክልሉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

የክልሉ ፕሬዚዳንት ተደርገው የተመረጡት  ድብርጺዮን ገ/ ሚካዔል (ዶ/ር)  ቃለ...

” ኢራን ከምድረ ገጽ ትጠፋለች ” – ትራምፕ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ቴሌቪዥን ጋር ቃለ...

የአርበኞች ድል መታሰቢያ እና የዛሬው ትውልድ ለሕብረት ያለው አቋም

የጥንት ኢትዮጵያዊያንአርበኞች ድል 85 ኛው ዓመት መታሰቢያ ሚያዚያ...