ትራምፕ ለሦስተኛ ጊዜ ለስልጣን ሊወዳደሩ እንደሚችሉ ተናገሩ

Date:

የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ሕገ መንግሥት የፕሬዚዳንትነት ስልጣን የሁለት ጊዜ ገደብ ቢኖርም፤ ለሦስተኛ የሥልጣን ዘመን ሊወዳደሩ እንደሚችሉ በድጋሚ ተናገሩ።  

ትራምፕ ከአሜሪካዉ «ኤንቢሲ» ዜና ወኪል ጋር በደረጉት ቆይታ “እየቀለድኩ አይደለም” ብለዋል።

ትራምፕ ይህን ህልማቸዉን ለማሳካት ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ዘዴዎችንም ጠቁሟል።

እንደ ትራምፕ በሕገ መንግሥቱ 22ኛው  አንቀጽ፤ ሕገ መንግሥታዊ ለውጥ ሳይደረግ ለሦስተኛ ጊዜ ለስልጣን መወዳደር በሕግ የማይቻል እንዲሆን ያደርጋል ብለዋል።

ትራምፕ ሁለተኛ የስልጣን ዘመናቸዉን ከያዙ በኋላ፣  የመንግስት ዘርፎች ላይ ለዉጥ ለማድረግ ከኤሎን ሙስክ ጋር ተባብሮ መስራትን ጨምሮ ታይቶ የማይታወቅ አስፈፃሚ እርምጃዎችን በመተግበር ላይ መሆናቸዉ ይታወቃል።

የትራምፕ ደጋጋፊዎች በበኩላቸዉ፤ በርታ ከዚህ በበለጠ  ማድረግ አለብህ እያሉ አበጀህ ሲሉ ጥሪ እያሰሙ ነዉ። 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን...

‹‹ሃገረ ትግራይ›› በዘመናት መነፅር ሲታይ

(አጭርዳሰሳ) በወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) የመጽሐፉርዕስ፡- ሃገረ ትግራይ የመጽሐፉ ዓይነት፡-...

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...