ትራምፕ ለሦስተኛ ጊዜ ለስልጣን ሊወዳደሩ እንደሚችሉ ተናገሩ

Date:

የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ሕገ መንግሥት የፕሬዚዳንትነት ስልጣን የሁለት ጊዜ ገደብ ቢኖርም፤ ለሦስተኛ የሥልጣን ዘመን ሊወዳደሩ እንደሚችሉ በድጋሚ ተናገሩ።  

ትራምፕ ከአሜሪካዉ «ኤንቢሲ» ዜና ወኪል ጋር በደረጉት ቆይታ “እየቀለድኩ አይደለም” ብለዋል።

ትራምፕ ይህን ህልማቸዉን ለማሳካት ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ዘዴዎችንም ጠቁሟል።

እንደ ትራምፕ በሕገ መንግሥቱ 22ኛው  አንቀጽ፤ ሕገ መንግሥታዊ ለውጥ ሳይደረግ ለሦስተኛ ጊዜ ለስልጣን መወዳደር በሕግ የማይቻል እንዲሆን ያደርጋል ብለዋል።

ትራምፕ ሁለተኛ የስልጣን ዘመናቸዉን ከያዙ በኋላ፣  የመንግስት ዘርፎች ላይ ለዉጥ ለማድረግ ከኤሎን ሙስክ ጋር ተባብሮ መስራትን ጨምሮ ታይቶ የማይታወቅ አስፈፃሚ እርምጃዎችን በመተግበር ላይ መሆናቸዉ ይታወቃል።

የትራምፕ ደጋጋፊዎች በበኩላቸዉ፤ በርታ ከዚህ በበለጠ  ማድረግ አለብህ እያሉ አበጀህ ሲሉ ጥሪ እያሰሙ ነዉ። 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...