የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ሕገ መንግሥት የፕሬዚዳንትነት ስልጣን የሁለት ጊዜ ገደብ ቢኖርም፤ ለሦስተኛ የሥልጣን ዘመን ሊወዳደሩ እንደሚችሉ በድጋሚ ተናገሩ።
ትራምፕ ከአሜሪካዉ «ኤንቢሲ» ዜና ወኪል ጋር በደረጉት ቆይታ “እየቀለድኩ አይደለም” ብለዋል።
ትራምፕ ይህን ህልማቸዉን ለማሳካት ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ዘዴዎችንም ጠቁሟል።
እንደ ትራምፕ በሕገ መንግሥቱ 22ኛው አንቀጽ፤ ሕገ መንግሥታዊ ለውጥ ሳይደረግ ለሦስተኛ ጊዜ ለስልጣን መወዳደር በሕግ የማይቻል እንዲሆን ያደርጋል ብለዋል።
ትራምፕ ሁለተኛ የስልጣን ዘመናቸዉን ከያዙ በኋላ፣ የመንግስት ዘርፎች ላይ ለዉጥ ለማድረግ ከኤሎን ሙስክ ጋር ተባብሮ መስራትን ጨምሮ ታይቶ የማይታወቅ አስፈፃሚ እርምጃዎችን በመተግበር ላይ መሆናቸዉ ይታወቃል።
የትራምፕ ደጋጋፊዎች በበኩላቸዉ፤ በርታ ከዚህ በበለጠ ማድረግ አለብህ እያሉ አበጀህ ሲሉ ጥሪ እያሰሙ ነዉ።
