ትራምፕ በጃፓን ላይ እስከ 35 በመቶ ታሪፍ ለመጣል ዛቱ

Date:

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለቱ አገራት መካከል የታሪፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ የተቀመጠው ቀነ ገደብ ከመጠናቀቁ በፊት መግባባት ላይ የማይደረስ ከሆነ በጃፓን ላይ “30 ወይም 35 በመቶ” ታሪፍ እንደሚጥሉ ዛቱ።

ይህም በፈረንጆቹ ሚያዝያ 2 ቀን በዓለም ዙሪያ ባሉ አገራት ላይ ከፍተኛ የገቢ ቀረጥ ባወጁበት ወቅት ጃፓን ላይ ከተጣለው የ24 በመቶ ታሪፍ የበለጠ ይሆናል።

በአብዛኞቹ የንግድ አጋሮች ላይ ተጥሎ የነበረው ታሪፍ ከዋሽንግተን ጋር የሚደራደሩበት ጊዜ ለመስጠት በሚል ለ90 ቀናት ወደ 10 በመቶ ዝቅ ብሎ ነበር።

ይህ የእፎይታ ጊዜ በሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ የሚገባደድ ሲሆን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀነ ገደቡን የማራዘም ሃሳብ እንደሌላቸው ተናግረዋል።

ትራምፕ ከቶኪዮ ጋር ስምምነት ላይ መድረስ ስለመቻሉ ጥራጣሬ አላቸው የቢቢሲ ዘገባ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...