ቻይንኛ ቋንቋን በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለመስጠት ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ ነዉ

Date:

ከቻይና መንግስት ጋር ባለው ግንኙነት መሰረት መስከረም ላይ በሚጀምረው የ2019 ትምህርት ዘመን በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የቻይንኛ ቋንቋ እንዲሰጥ ለማድረግ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በእነዚህ ትምህርትቤቶች ውስጥ ቻይንኛን የሚያስተምሩ መምህራንን ለማስመጣትም ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል።

በትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ አስራአስፈፃሚ ዶ/ር ዮሀንስ ወጋሶ የአዳሪ ትምህርትቤት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያላቸውና በመለያ ፈተና አልፈው የሚገቡ መሆናቸውን አንስተዋል።

እነዚህ ተማሪዎች በአለምአቀፍ ደረጃ ውጤታማና ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግም የተለያዩ የውጪ ሀገር ቋንቋዎችን እንዲማሩ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

በተለይም ደግሞ ተማሪዎች የከፍተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በውጪ ሀገር የመከታተል እድል ያላቸው በመሆኑ ለዛ እንዲጠቅማቸው የቋንቋ ትምህርቱ እንደሚሰጥ አመላክተዋል።

እንዲማሩ ከሚደረጉት ቋንቋዎች መካከል ደግሞ በቀጣዩ የ2019 የትምህርት ዘመን የቻይንኛ ቋንቋን እንዲማሩ ለማስቻል የዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከቻይንኛ በተጨማሪም ሌሎች አለምአቀፍ ቋንቋዎችን በማጠናከር የማስተማር ስራው እንደሚቀጥል ዶ/ር ዮሀንስ አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ካናዳ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል"...

የክቡር ዶክተር ጋሽ መሐሙድ አዲስ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነዉ

ታዋቂው ድምፃዊ ክቡር ዶክተር አርቲስት መሐሙድ አሕመድ «ለታሪክ» የተሰኘውንና...

ሜታ ‘ፌስቡክ እና ኢንስታግራም በቀረበባቸው ክስ 18 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ

ግዙፉ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያ ሜታ በፌስቡክ እና በኢንስታግራም ምክንያት...