ኃላፊነት የጎደለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና መፍትሄዎቹ…

Date:

ከባህል፣ ከእሴትና ሥነምግባር ያፈነገጠ ኃላፊነት የጎደለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም መፍትሄ ሊበጅለት ይገባል አሉ ምሁራን።

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ያነጋገራቸው ምሁራን ከባህልና እሴት ያፈነገጡ ይዘቶችን የሚያጋሩ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪዎች መበራከት አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በጅማ ዩኒቨርስቲ ሶሺዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ነጋ ጂባት (ዶ/ር) እንደሚሉት፥ ጥቂት የማይባሉ በርካታ ተከታዮችን ማፍራት የቻሉ ይዘት ፈጣሪዎች አፈንጋጭ የሆኑ ይዘቶችን በማጋራት በትውልድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራሉ፡፡

አሉታዊ ይዘቶች ህብረተሰቡ ላይ ማህበራዊና ስነልቦናዊ ጉዳት እንደሚያስከትሉ ገልጸው፥ ለትውልድ መልካም አርዓያ ስላልሆኑ እልባት ሊበጅላቸው ይገባል ነው ያሉት፡፡

በጅማ ዩኒቨርስቲ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጥናት ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ጌታቸው ጥላሁን (ዶ/ር) በበኩላቸው የዲጂታል አለም መስፋት የሚበረታታ ቢሆንም፥ ይዘት ፈጣሪዎች በህጋዊና በተጠየቅ መልኩ እሴትን አክብረው ማገልገል አለባቸው ብለዋል።

የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ምሁራንና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችም ቢሆኑ በተቀደደው ቦይ ከመፍሰስ ይልቅ በዘርፉ እርምት እንዲወሰድ የሚጠበቅባቸውን ሚና በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ ጠቁመው፥ የሚዲያን አጠቃቀም ከስር ጀምሮ ማስተማር እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...