አል ዐይን አማርኛ ሥራ ሊያቆም ነው

Date:

ባለቤትነቱ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት የኾነው አል ዐይን አማርኛ የበይነ መረብ የዜና ማሠራጫ ሥራ ሊያቆም ነው ፡፡

የዜና ማሠራጫው በአማርኛ ቋንቋ ዜናዎችንና ዘገባዎችን የሚያዘጋጁ የኢትዮጵያ ዘጋቢዎቹን የቅጥር ውል አቋርጧል ፡፡

ተቋሙ የሠራተኞቹን ውል ያቋረጠው፣ የአማርኛ ዜና አገልግሎቱን አቁሞ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ለመውጣት በማሰቡ መኾኑን ተዘግቧል፡፡

ዘጋቢዎቹ ሥራቸውን እየሠሩ ባሉበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቂያ ሳይደርሳቸው፣ በድንገት የሥራ ውላቸው መቋረጡን የሚያመላክት መልዕክት በኢሜይል እንደደረሳቸው ዋዜማ ሰምታለች፡፡

ከአምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የዜና አገልግሎት የጀመረው አል ዐይን አማርኛ ከትናት በስትያ ጀምሮ ዜናዎችን አላሠራጨም፡፡ የዜና ድረረገጹ በዋናነት ትኩረቱን በመካከለኛው ምሥራቅ ላይ አድርጎ የአገር ውስጥና ዓለማቀፍ ዜናዎችን በአማርኛ ቋንቋ ለኢትዮጵያዊን አንባቢዎች ሲያቀርብ ነበር ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንና የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ...

አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ አዲስ መግለጫ አወጣች

ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ...

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...