አል ዐይን አማርኛ ሥራ ሊያቆም ነው

Date:

ባለቤትነቱ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት የኾነው አል ዐይን አማርኛ የበይነ መረብ የዜና ማሠራጫ ሥራ ሊያቆም ነው ፡፡

የዜና ማሠራጫው በአማርኛ ቋንቋ ዜናዎችንና ዘገባዎችን የሚያዘጋጁ የኢትዮጵያ ዘጋቢዎቹን የቅጥር ውል አቋርጧል ፡፡

ተቋሙ የሠራተኞቹን ውል ያቋረጠው፣ የአማርኛ ዜና አገልግሎቱን አቁሞ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ለመውጣት በማሰቡ መኾኑን ተዘግቧል፡፡

ዘጋቢዎቹ ሥራቸውን እየሠሩ ባሉበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቂያ ሳይደርሳቸው፣ በድንገት የሥራ ውላቸው መቋረጡን የሚያመላክት መልዕክት በኢሜይል እንደደረሳቸው ዋዜማ ሰምታለች፡፡

ከአምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የዜና አገልግሎት የጀመረው አል ዐይን አማርኛ ከትናት በስትያ ጀምሮ ዜናዎችን አላሠራጨም፡፡ የዜና ድረረገጹ በዋናነት ትኩረቱን በመካከለኛው ምሥራቅ ላይ አድርጎ የአገር ውስጥና ዓለማቀፍ ዜናዎችን በአማርኛ ቋንቋ ለኢትዮጵያዊን አንባቢዎች ሲያቀርብ ነበር ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...