አሜሪካ በሶሪያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተከትሎ የተለያዩ ተቋማትና ሀገራት ምን አሉ?

Date:

የተመድ ዋና ፀሐፊ ቃል አቀባይ ስቴቨን ዱጃሪች፣ “አሜሪካ በሶሪያ የጣለቻቸውን ማዕቀቦች ማንሳቷ የሶሪያን ህዝብ የአኗኗር ዘይቤ ይቀይራል” ብለዋል።

የሶሪያ ቻምበር ኦፍ ኮሜርስ፣ “የማዕቀቡ መነሳት ኢኮኖሚስቶች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያበረታታል” ሲል ገልጿል።

የሶሪያ የኢኮኖሚና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ “የሶሪያ ኢኮኖሚ እንደ አዲስ እንዲያንሰራራ አስተዋጽኦ ያደርጋል” ባይ ናቸው።

ኳይት በበኩሏ፣ “ውሳኔውን እደግፋለሁ” ስትል ገልጻለች።

የኦማን ሱልጣን የማዕቀቡን መነሳት፣ “የሚበረታታ ነው” ብለውታል።

የመን ማዕቀቡ መነሳቱ ጥሩ እርምጃ መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ገልጻለች።

የሊቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “ለጉዳት የተጋለጠውን የሶሪያን ህዝብ ከችግር ለማውጣት የተወሰደ አወንታዊ እርምጃ ነው” ሲል ውሳኔውን ደግፏል።

የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “አሜሪካ ማዕቀቡን ለማንሳት ያሳየችውን ድጋፍ እንደሚያደንቅ” ገልጿል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላምና ብልፅግናን ማዬት እንፈልጋለን” ሲል አስታውቋል።  

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ውጭ ምንዛሪ የሚያድኑ የሴራሚክ ምርቶች በቅርቡ ለገበያ ይቀርባሉ

ይህ የተገለፀው ኢትዮደር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በ”Golden Tier...

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...