አሜሪካ በሶሪያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተከትሎ የተለያዩ ተቋማትና ሀገራት ምን አሉ?

Date:

የተመድ ዋና ፀሐፊ ቃል አቀባይ ስቴቨን ዱጃሪች፣ “አሜሪካ በሶሪያ የጣለቻቸውን ማዕቀቦች ማንሳቷ የሶሪያን ህዝብ የአኗኗር ዘይቤ ይቀይራል” ብለዋል።

የሶሪያ ቻምበር ኦፍ ኮሜርስ፣ “የማዕቀቡ መነሳት ኢኮኖሚስቶች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያበረታታል” ሲል ገልጿል።

የሶሪያ የኢኮኖሚና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ “የሶሪያ ኢኮኖሚ እንደ አዲስ እንዲያንሰራራ አስተዋጽኦ ያደርጋል” ባይ ናቸው።

ኳይት በበኩሏ፣ “ውሳኔውን እደግፋለሁ” ስትል ገልጻለች።

የኦማን ሱልጣን የማዕቀቡን መነሳት፣ “የሚበረታታ ነው” ብለውታል።

የመን ማዕቀቡ መነሳቱ ጥሩ እርምጃ መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ገልጻለች።

የሊቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “ለጉዳት የተጋለጠውን የሶሪያን ህዝብ ከችግር ለማውጣት የተወሰደ አወንታዊ እርምጃ ነው” ሲል ውሳኔውን ደግፏል።

የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “አሜሪካ ማዕቀቡን ለማንሳት ያሳየችውን ድጋፍ እንደሚያደንቅ” ገልጿል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላምና ብልፅግናን ማዬት እንፈልጋለን” ሲል አስታውቋል።  

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...