በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ መርሃ ግብር አርሰናል ሪያል ማድሪድን 3 ለ 0 አሸንፏል።
መድፈኞቹን አሸናፊ ያደረጉ ጎሎችን ዴክላን ራይስ (2) እና ሚኬል ሜሪኖ በ2ኛው አጋማሽ አስቆጥረዋል።
ካማቪንጋ በሪያል ማድሪድ በኩል በጨዋታው መጠናቀቂያ በ2 ቢጫ ከሜዳ ተሰናብቷል።
በሌላ የምሽቱ መርሃ ግብር ኢንተር ሚላን ከሜዳው ውጭ ባየርን ሙኒክን 2 ለ 1 አሸንፏል።
ለኢንተር ጎሎቹን ላውታሮ ማርቲኔዝና ፍራቴሲ ሲያስቆጥሩ፥ ባለሜዳዎቹን ሙኒኮች ከሽንፈት ያልታደገችውን ጎል ቶማስ ሙለር ከመረብ አሳርፏል።
