የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በክልሉ ወቅታው ሁ
👉 የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል የሚያደርጋቸውን በጎ ስራዎች መጥቀስ በህወሓት ቡድን ዘንድ ተቀባይነት የሚያሳጣና በባንዳነት የሚያስፈርጅ ነው፣
👉 ይህ ኃይል የትግራይን ህዝብ የሰላምና የልማት አጀንዳ ነጥቆ የግርግርና የትርምስ አጀንዳ በመፍጠሩ ህዝቡ መስቀለኛ መንገድ ላይ እንዲቆም አድርጓል፣
👉 ሁሉም የትግራይ ህዝብ ህልውና የሚገደውና ለኢትዮጵያ ይጠቅማል ብሎ የሚያምን ህዝቡ ካጋጠመው ቀውስ እንዲወጣ የሚቻለውን ማድረግ አለበት፣
👉 የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዓላማዎች በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን ማረጋገጥ፣ ለክልሉ የኢኮኖሚ መልሶ ግንባታ መሰረት መጣል፣ ቀጣይ ምርጫ እስከሚካሄድ ድረስ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወን ነው፣
👉 በክልሉ የተፈጠረው አለመረጋጋት የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋምና ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስ ስራ ላይ እክል ፈጥሯል፣
👉 ከ75 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የተቋረጠው የመልሶ የማቋቋም ሂደት እንዲቀጥል እየጠየቁ ነው፣
👉 የፕሪቶሪያው ስምምነት ዓላማ ተኩስ ማቆም ነው፤ የፕሪቶሪያ ስምምነት በተሟላ ሁኔታ ከተተገበረ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሳይሆን በህዝብ የተመረተ መንግስት ነው ሊኖር የሚገባው፣
👉 የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋምና ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው፤ ለዚህ የፌደራል መንግስትም የበኩሉን ሚና መወጣት አለበት፣
👉 ትግራይ ውስጥ ያለው የጸጥታ ኃይል ስልጣንን ብቻ ማዕከል ያደረገው ትንሽ አባላት ያሉት ቡድን በሚፈጥረው ትርምስ ውስጥ መግባት አይፈልግም፣
👉 ከሻዕቢያ ጋር ግንኙነት ያላቸው የህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አካላት አሉ፤ ይህ ግንኙነት የትግራይን ህልውና እና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ አይጠቅምም፣
👉 በህወሓት ኃይሎች መካከል ለተፈጸመው ጥፋት የፌደራል መንግስትን ተጠያቂ ማድረግ አግባብ አይደለም።
