አቶ ጌታቸው ረዳ ትላንት በክልሉ ወቅታው ሁኔታ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ላይ ያነሷቸው አንኳር ነጥቦች፦

Date:

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በክልሉ ወቅታው ሁ

👉 የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል የሚያደርጋቸውን በጎ ስራዎች መጥቀስ በህወሓት ቡድን ዘንድ ተቀባይነት የሚያሳጣና በባንዳነት የሚያስፈርጅ ነው፣

👉 ይህ ኃይል የትግራይን ህዝብ የሰላምና የልማት አጀንዳ ነጥቆ የግርግርና የትርምስ አጀንዳ በመፍጠሩ ህዝቡ መስቀለኛ መንገድ ላይ እንዲቆም አድርጓል፣

👉 ሁሉም የትግራይ ህዝብ ህልውና የሚገደውና ለኢትዮጵያ ይጠቅማል ብሎ የሚያምን ህዝቡ ካጋጠመው ቀውስ እንዲወጣ የሚቻለውን ማድረግ አለበት፣

👉 የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዓላማዎች በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን ማረጋገጥ፣ ለክልሉ የኢኮኖሚ መልሶ ግንባታ መሰረት መጣል፣ ቀጣይ ምርጫ እስከሚካሄድ ድረስ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወን ነው፣

👉 በክልሉ የተፈጠረው አለመረጋጋት የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋምና ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስ ስራ ላይ እክል ፈጥሯል፣

👉 ከ75 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የተቋረጠው የመልሶ የማቋቋም ሂደት እንዲቀጥል እየጠየቁ ነው፣

👉 የፕሪቶሪያው ስምምነት ዓላማ ተኩስ ማቆም ነው፤ የፕሪቶሪያ ስምምነት በተሟላ ሁኔታ ከተተገበረ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሳይሆን በህዝብ የተመረተ መንግስት ነው ሊኖር የሚገባው፣

👉 የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋምና ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው፤ ለዚህ የፌደራል መንግስትም የበኩሉን ሚና መወጣት አለበት፣

👉 ትግራይ ውስጥ ያለው የጸጥታ ኃይል ስልጣንን ብቻ ማዕከል ያደረገው ትንሽ አባላት ያሉት ቡድን በሚፈጥረው ትርምስ ውስጥ መግባት አይፈልግም፣

👉 ከሻዕቢያ ጋር ግንኙነት ያላቸው የህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አካላት አሉ፤ ይህ ግንኙነት የትግራይን ህልውና እና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ አይጠቅምም፣

👉 በህወሓት ኃይሎች መካከል ለተፈጸመው ጥፋት የፌደራል መንግስትን ተጠያቂ ማድረግ አግባብ አይደለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...