ኡጋንዳ ከኢትዮጵያ፣ ከሶማሊያ እና ከኤርትራ የሚመጡ አዲስ ስደተኞች መቀበል አቆመች

Date:

ሪፊውጂስ ኢንተርናሽናል የተሰኘው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፣ ኡጋንዳ ከኢትዮጵያ፣ ከሶማሊያ እና ከኤርትራ ለሚመጡ አዲስ ስደተኞች የስደተኛነት መብት መስጠቷን ማቆሟን “አሳሳቢ እርምጃ” ሲል አውግዟል።

ድርጅቱ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በዜግነት ላይ ብቻ ተመስርቶ ጥገኝነትን መከልከል የዓለም አቀፍ የስደተኞች ሕግን የሚጥስ ሲሆን፣ አዲሱ ገደብ እነዚህን ስደተኞች ሕጋዊ አጣብቂኝ ውስጥ በመክተት ለከፋ ብዝበዛና ጥቃት ይዳርጋቸዋል።

ይህ ውሳኔ ኡጋንዳ ቀደም ሲል ስደተኞችን በመቀበል ያላት ኩሩ ልማድ የሚጻረር መሆኑም ተገልጿል።

ሪፊውጂስ ኢንተርናሽናል፣ ኡጋንዳ የደረሰባት ከፍተኛ የእርዳታ ቅነሳ የጥገኝነት ሥርዓቷን ችግር ውስጥ መክተቱን አምኗል።

በተለይም ዩናይትድ ስቴትስ የጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ኡጋንዳ ለመላክ ስምምነት ብትፈርምም፣ የራሷን እርዳታ መቀነሷ ለችግሩ መባባስ ምክንያት መሆኑን ድርጅቱ አመልክቷል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ፣ ለዓመታት ኡጋንዳን ሲያሞግሱ የቆዩ ለጋሽ መንግሥታት አሁን ቃላቸውን ለስደተኞችም ሆነ ለአስተናጋጅ ማኅበረሰቦች በሚሰጡት ተጨባጭ ድጋፍ በማረጋገጥ፣ ኡጋንዳ የገጠማትን የገንዘብ ችግር እንዲያቀልሉ ጥሪ አቅርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...