ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

Date:

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች ኢራንን ለመደብደብ ከአገራቸው ይነሱ እንደነበር ተናገሩ ።

ዩናይትድ ስቴትስ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ግድም ኢራንን ዳግም ስትደበድብ ቆይታ በድንገት ድብደባውን ባለፈው ዐርብ ጋብ አድርጋ አቋርጣለች ። በሁለት ሣምንቱ የኢራን ድብደባ እሥራኤል እንደ ከዚህ ቀደሙ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ተባብራ ድብደባ አልፈጸመችም ።

ምድሯን ለዩናይትድ ስቴትስ ጦር ጄቶች ክፍት በማድረጓ ለሚደርስባት ማናቸውም ጥቃት የአጸፌታ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መኾኗንም ይፋ አድርጋለች ።

የእሥራኤል ጠቅላይ ሚንሥትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ አገራቸው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በጋራ ኢራን ላይ ጦርነት ከከፈተችበት ጊዜ አንስቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ይመክራሉ ተብሏል ።

እሥራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ ከሔዝቦላህ ጋር የነበራቸውን ጦርነት በተመለከተ ከሊባኖስ ጋር ስለደረሱበት ስምምነትም ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...