“ኢራንን መምታት  አደጋ ነው” ቻይና

Date:


ቻይና” በመካከለኛው ምስራቅ ሰማይ ላይ የጦርነት” ዳመና” ሲያንዣብብ እየታየኝ ነው”  ስትል አስጠነቀቀች።

በመንግስታቱ ድርጅት የቻይና ምክትል ቋሚ ተወካይ በኢራን ዙሪያ ውጥረት እንዲነግስ ማድረግ መካከለኛው ምስራቅን ወደ ግጭት እንደማስገባት ነው ብለዋል።

አሜሪካ በሀይል ጫና ለማሳደር የምትሄድበትን ርቀት እንድታለዝበው ጥሪ አቅርበዋል ተወካዩ።

ሁሉም አካላት ውጥረቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ ቤይጂንግ በመንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ጥያቄዋን አቅርባለች።

ዋሽንግተን በግልፅ ቴህራንን ልትመታ እንደምትችል በተደጋጋሚ መግልጫ እያወጣች ነው ፣ ይህም ሰላም አያመጣም በሚልም ቤይጂንግ ከሳለች።

ቻይና ወታደራዊ አማራጮችን እንደማትቀበልም በምክር ቤቱ አረጋግጣለች።

ሀይል መጠቀም ለችግሮች  ፈፅሞ መፍትሄ አያመጣም ቻይና ስትል የሩሲያ ተወካይ በበኩላቸው አሜሪካ የኢራንን የውስጥ ጉዳይ ለፖለቲካዋ እየተጠቀመችበት ነው ሲሉ በፀጥታው ምክር ቤት  ወቅሰዋል።

ዘገባው የአልጀዚራ ነው

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...