ቻይና” በመካከለኛው ምስራቅ ሰማይ ላይ የጦርነት” ዳመና” ሲያንዣብብ እየታየኝ ነው” ስትል አስጠነቀቀች።
በመንግስታቱ ድርጅት የቻይና ምክትል ቋሚ ተወካይ በኢራን ዙሪያ ውጥረት እንዲነግስ ማድረግ መካከለኛው ምስራቅን ወደ ግጭት እንደማስገባት ነው ብለዋል።
አሜሪካ በሀይል ጫና ለማሳደር የምትሄድበትን ርቀት እንድታለዝበው ጥሪ አቅርበዋል ተወካዩ።
ሁሉም አካላት ውጥረቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ ቤይጂንግ በመንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ጥያቄዋን አቅርባለች።
ዋሽንግተን በግልፅ ቴህራንን ልትመታ እንደምትችል በተደጋጋሚ መግልጫ እያወጣች ነው ፣ ይህም ሰላም አያመጣም በሚልም ቤይጂንግ ከሳለች።
ቻይና ወታደራዊ አማራጮችን እንደማትቀበልም በምክር ቤቱ አረጋግጣለች።
ሀይል መጠቀም ለችግሮች ፈፅሞ መፍትሄ አያመጣም ቻይና ስትል የሩሲያ ተወካይ በበኩላቸው አሜሪካ የኢራንን የውስጥ ጉዳይ ለፖለቲካዋ እየተጠቀመችበት ነው ሲሉ በፀጥታው ምክር ቤት ወቅሰዋል።
ዘገባው የአልጀዚራ ነው
