ኢራን አሜሪካ ላደረሰችው የአየር ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ሰጠች

Date:

ኢየኢራን አብዮታዊ ዘብ ( አይ አር ጂ ሲ) የባህር እና ኤሮስፔስ ኃይል በጥምረት የሚሳዔል እና ሰው አልባ አውሮፕላን ዘመቻ አድርጎ 85 ወሳኝ የአሜሪካን ጦር ሰፈሮች እንዲሁም ቁልፍ ዒላማዎችን መምታቱን አሳውቋል፡፡

ዋሽንግተን በገሽም ፣ባንዳር አባስ፣እና ሲሪክ ላይ ኃይለኛ ጥቃት በማዕከላዊ ዕዟ በኩል ከፈጸመች በኋላ የተሰነዘረ የቴህራን ጥቃት ነው ፡፡

አይ አር ጂ ሲ በአሜሪካው ፊፍዝ ፍሊት (የጦር ምድብ ) በባህሬን እንዲሁም በአሊ-አል ሳሌም የአየር ኃይል ጦር ሰፈር በኩዌት አደገኛውን ጥቃት ማድረሱን አሳውቋል ፡፡

አሜሪካ ተኩስ አቁምን በመጣሷ የተሰጠ ምላሽ ነው ያለችው ቴህራን አሁንም እርምጃዋን አጠናክራ ልትቀጥል እንደምትችል አስጠንቅቃለች ፡፡

ምንም እንኳን አሜሪካ በወታደራዊ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት አድርሻለሁ ብትልም ፤ኢራን ጉዳቱ ያን ያህል አልበረታብኝም በሚል አስተባብላለች፡፡

በባህር ዳርቻዎች ፣ በሆርሞጋን እና ማህሻህር አካባቢዎች ጥቃት መድረሱም ይፋ ሆኗል ፡፡

አሜሪካ እና ኢራን ዳግም ወደ ውጥረት ውስጥ መግባታቸው የአያቶላህ አሊ ኻሚኒን የሽኝት ስነ -ስርዓት ጥቁር ጥላ ያጠላበታልም ተብሏል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...

እናት ፓርቲ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን “የእነ አጼ በጉልበቱ መፈንጫ” ሲል ኮነነ ውጤቱንም እንደማይቀበል አስታወቀ

እናት ፓርቲ በቅርቡ የተካሄደውን የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ አጠቃላይ ሂደትና...