ኢራን የኒኩሌር ስምምነት ካላደረገች መከራ  ይዘንብባታል

Date:



የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ኒኩሌር ስምምነት ድርርድር እንድትመለስ አስጠነቀቁ ፥ ያ ካልሆነ ብርቱ ወታደራዊ ጥቃት ሊከተል እንደሚችል ዝተዋል ።

ፕሬዚደንቱ ሶሻል ትሩዝ በተሰኘው የግል የማኅበራዊ መገናኛ መድረካቸው ዛሬ ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ «ጊዜው እያከተመ ነው» ብለዋል ።

ኢራን ቀደም ሲል ከእኔ ጋር ስምምነት ባለመፈጸሟ «ተልእኮ የእኩለ ሌሊት መዶሻ» የተሰኘው እጅግ ብርቱ ጥቃት ነው የደረሰባት ያሉት ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ያሁኑ የከፋ ይሆናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል ። 

ባለፈው ኢራን ከሥራኤል ጋር ለ12 ቀናት ባደረገችው ጦርነት በ«ተልእኮ የእኩለ ሌሊት መዶሻ» የኢራን የአቶም ተቋምን የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከራዳር ዕይታ ውጪ በመብረር በቦንብ ደጋግመው ደብድበው ነበር ።

«አማንዳ» የተሰኘችው የዩናይትድ ስቴትስ በርካታ የጦር ጄቶች ተሸካሚ ግዙፍ የጦር መርከብም ወደ ኢራን አቅጣጫ እየቀዘፈች መሆኑን ዶናልድ ትራምፕ ተናግረው ነበር ።

የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር መሥሪያ ቤት በበኩሉ የዩናይትድ ስቴትስ ሥጋት ከቀጠለ በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ድርድር ሊኖር እንደማይችል አሳውቋል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...