የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ኒኩሌር ስምምነት ድርርድር እንድትመለስ አስጠነቀቁ ፥ ያ ካልሆነ ብርቱ ወታደራዊ ጥቃት ሊከተል እንደሚችል ዝተዋል ።
ፕሬዚደንቱ ሶሻል ትሩዝ በተሰኘው የግል የማኅበራዊ መገናኛ መድረካቸው ዛሬ ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ «ጊዜው እያከተመ ነው» ብለዋል ።
ኢራን ቀደም ሲል ከእኔ ጋር ስምምነት ባለመፈጸሟ «ተልእኮ የእኩለ ሌሊት መዶሻ» የተሰኘው እጅግ ብርቱ ጥቃት ነው የደረሰባት ያሉት ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ያሁኑ የከፋ ይሆናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል ።
ባለፈው ኢራን ከሥራኤል ጋር ለ12 ቀናት ባደረገችው ጦርነት በ«ተልእኮ የእኩለ ሌሊት መዶሻ» የኢራን የአቶም ተቋምን የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከራዳር ዕይታ ውጪ በመብረር በቦንብ ደጋግመው ደብድበው ነበር ።
«አማንዳ» የተሰኘችው የዩናይትድ ስቴትስ በርካታ የጦር ጄቶች ተሸካሚ ግዙፍ የጦር መርከብም ወደ ኢራን አቅጣጫ እየቀዘፈች መሆኑን ዶናልድ ትራምፕ ተናግረው ነበር ።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር መሥሪያ ቤት በበኩሉ የዩናይትድ ስቴትስ ሥጋት ከቀጠለ በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ድርድር ሊኖር እንደማይችል አሳውቋል ።
ኢራን የኒኩሌር ስምምነት ካላደረገች መከራ ይዘንብባታል
Date:
