ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር 3ኛ ወጡ

Date:

በካናዳ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ የተሳተፉት የኢትዮ ሮቦቲክስ ታዳጊዎች 3ኛ በመውጣት አገርን የሚያኮራ አስደማሚ ድል አስመዝገቡ።

ከውድድሩ አስቀድሞ በ”ታዲያስ አዲስ” ፕሮግራም የአውሮፕላን ቲኬት እና የሆቴል ወጪ ድጋፍ በተደረገለት ተማሪ አማካኝነት የተገኘው ይህ ድል፣ የኢትዮጵያን ስም በዓለም አቀፍ መድረክ በድምቀት ማስጠራት ችሏል።

ኢትዮ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል ላለፉት 15 ዓመታት ታዳጊና ወጣቶችን በኮዲንግ፣ ዲዛይኒንግ እና ኢንጂነሪንግ በማሰልጠን ለቴክኖሎጂው ዓለም ሲያዘጋጅ የቆየ ተቋም ነው።

በአዲስ አበባ 4 ማዕከሎችን ከፍቶ ስልጠናውን በመስጠት ላይ የሚገኘው ማዕከሉ፣ በቀጣይ ወደ ኮሌጅ ደረጃ ለማደግ በሂደት ላይ መሆኑ ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢትዮጵያዊዉ የመጀመሪያው የአይን ሐኪም ዶክተር ጳውሎስ አረፉ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዓይን ሐኪም እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓይን...

ሁቲዎች የሳዑዲ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ገለጹ

የኢራን አጋር የሆኑት ሁቲዎች የሳዑዲ አራምኮ ጃዛን ነዳጅ ማጣሪያን...

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝች

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ጽጋብ እና ሽቶ...

“አዳም አንድ ደራሲ የሚያስፈልጉት ሁሉም ግብዓቶች ተሟልተው ያሉት ፀሐፊ ነው”

አዳም ረታ ሥራዎቹን ለአንባቢ ማድረስ የጀመረው ከ1970ዎቹ አንስቶ ነው።...