ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በኢዩጂን ዳይመንድ ሊግ ውድድር

Date:

ትናንት በኢዩጂን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉበት የወንዶች 10 ሺህ ሜትር ፣የሴቶች 5 ሺህ ፣800 ሜትር እና 1500 ሜትር ውድድር ተካሂዷል ።

በወንዶች 10ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ 1-3 በመውጣት ድል ተቀዳጅቷል ።

አትሌት ቢኒያም መሀሪ ውድድሩን በ 26:43.82 በመግባት ሲያሸንፍ ፣አትሌት በሪሁ አረጋዊ 26:43.84 በመግባት ሁለተኛ ሲወጣ
አትሌት ሰለሞን ባረጋ 26: 44.13 በሆነ ሰዓት ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል ።

በ5ሺህ ሴቶች ውድድር የፓሪስ ኦሎምፒክ የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ሻምፒዮናዋ ቢያትሪስ ችቤት የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር አሸንፋለች ።

አትሌት ቢያትሪስ ችቤት 13:58.06 በመግባት በአትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን አሻሽላለች ።

በውድድሩ ላይ ኬንያዊቷ አትሌት ንጌቲች ሁለተኛ ስትወጣ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ14:04.41 ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

በ800 ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት ፅጌ ዱግማ 1:57.10 በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች ።

በ1500 ሜትር ውድድር ኬንያዊቷ አትሌት ፌዝ ኪፒዮጎን በ3:48.68 በመግባት በራሷ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፋለች።

በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው አትሌት ድርቤ ወልተጂ በ3:51.44 በመግባት ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቃለች ።

በሌላ ዜና በፈረንሳይ ናንሲ በተካሄደው የ800 ሜትር የሴቶች ውድድር አትሌትንግስት ጌታቸው 1:58.15 በመግባት ስታሸንፍ፣ በወንዶች ውድድር አትሌት ዮሐንስ ተፈራ 1:44.49 በመግባት ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን...

‹‹ሃገረ ትግራይ›› በዘመናት መነፅር ሲታይ

(አጭርዳሰሳ) በወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) የመጽሐፉርዕስ፡- ሃገረ ትግራይ የመጽሐፉ ዓይነት፡-...

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...