የእስራኤል መከላከያ ኃይል ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል ኤፊ ዴፍሪን እንደተናገሩት ዘመቻው ከዚህ ቀደም ከነበሩት ጥቃቶች በተለየ መልኩ ሐማስ እንደገና ቁጥጥር እንዳያገኝ ግዛትን በማስጠበቅ ላይ ያተኩራል።
“እየገፋን ነው፤ እና እኛን ሊያቆመን የሚችለው ብቸኛው ነገር የታጋቾቹ ወደ ቤታቸው መመለስ ብቻ ነው” ብለዋል።
ባለሥልጣኑ ንፁሀን ሰዎች ወደ “አስተማማኝ ቦታዎች” እንደሚላኩ ገልፀዋል።
እስራኤል ለሁለት ወራት ያህል ምንም ዓይነት የሰብዓዊ እርዳታ እንዳይገባ ከከለከልች በኋላ እሁድ እለት “ወታደራዊ ዘመቻዎችን ማስፋት አስፈላጊ” በመሆኑ ምክንያት የጋዛ ነዋሪዎች “መሠረታዊ የምግብ መጠን” እንደሚያገኙ አስታውቃለች
