ከፋታ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተቋም ለ 38ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች በትላንትናው ቀን አስመረቀ

Date:

የከፋታ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተቋም ለ 38ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በትላንትናው ቀን ግንቦት-10-2017 ዓ.ም በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል አስመርቋል።

“ውበት በልዩነት በጋዜጠኝነት” በሚል መሪ ቃል የምረቃ ስነ-ስርዓታቸውን በ 6 ወር ጊዜ ውስጥ የተማሩትን ትምህርት በተግባር መድረክ ላይ በተለያዩ ፕሮግራሞች ለእንግዶች በማቅረብ አካሂደዋል።

በፕሮግራሙ ላይም አንጋፍ ጋዜጠኞች ተጋባዥ እንግዶች መምህራን እና የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

ተጋባዥ እንግዶች እና መምህራንም ለተመራቂ ተማሪዎች የ አደራ መልዕክት እና ምክር አስተላልፈዋል።

ከፋታ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተቋም በ 6 ወር የስልጠና ጊዜ መሠረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና በመስጠት ተማሪዎችን አሰልጥኖ በሙያዉ ብቁ በማድረጉ ረገድ ከፍተኛ የሆነ አስተዋፅኦ እያበረከተ የሚገኝ ተቋም ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...