እስራኤል በጋዛ የዘር ማጥፋት እየፈጸመች ነው

Date:

ሁለት ስመ ጥር የእስራኤል የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እስራኤል ጋዛ ውስጥ በፍልስጤማውያን ላይ የዘር ማጥፋት እየፈጸመች እንደሆኑ አስታወቁ።

‘ቤትሰሌም’ እና ‘ፊዚሻን ፎር ሂውማን ራይትስ እስራኤል’ የተሰኙት በእስራኤል ተቀማጭነታቸውን ያደረጉ ተቋማት የጋዛን ጦርነት አስመልክቶ ባወጡት ሪፖርት እስራኤል በፍልስጤም ሕዝብ ላይ እየፈጸመችው ያለው ድርጊት በዘር ፍጅትነት የሚፈረጅ ነው ብለዋል።

የመብት ቡድኖቹ ያለፉትን 21 ወራት የጋዛ ጦርነት አስመልክቶ ያደረጓቸውን ጥናቶች ሰኞ፣ ሐምሌ 21/2017 ዓ.ም ይፋ አድርገዋል።

በእስራኤል ውስጥ መቀመጫቸውን ለአስርት ዓመታት ያደረጉት እና በንቁ ተሳትፏቸው የሚታወቁት ተቋማቱ በጋራ ባወጡት መግለጫ “ወንጀሎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጥሪ ከማድረግ በተጨማሪ፤ በዚህ የጨለማ ወቅት ድርጊቶችን በስማቸው መጥራት መሠረታዊ ጉዳይ ነው” ብለዋል።

እስራኤላውያኑ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች አገራቸው “በፍልስጤማውያኑ ላይ የዘር ፍጅት እየፈጸመች ነው” በሚል ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጡትን ሪፖርት የእስራኤል መንግሥት ቃል አቀባይ ውድቅ አድርገውታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...