እንኳን ለ1 ሺህ 500ኛው የነብዩ መሐመድ መውሊድ መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ

Date:

ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 500ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ በማለት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መልካም ምኞቱን አስተላልፏል።

የዘንድሮ መውሊድ በሁለት ታላላቅ ክስተቶች መሐል የሚከበር በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ያለው ተቋሙ፤ የመጀመሪያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በየደረጃው የሚገኙ የምክር ቤቱ ድርጅታዊ መዋቅር ምርጫ ተከናውኖ ወደ መቋጫው በደረሰበት ወቅት መከበሩ ነው ብሏል፡፡

ሌላው ደግሞ የአንድነታችን ምሰሶና የሕብረታችን ማሳያ፣ የጥረት፣ የጽናት እና የትብብር ምሳሌና ምልክት የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ የምረቃ ጊዜውን በጉጉት በምንጠባበቅበት ሰሞን መከበሩ ነው ሲል ገልጿል።

የ1 ሺህ 500ኛው የመውሊድ በዓል ሲከበር በተለመደው ኢትዮጵያዊ የመረዳዳት ባህል ሊሆን እንደሚገባ እንዲሁም በሕመም አልጋ ላይ እና በሕግ ጥላ ስር የሚገኙትን ወገኖቻችንን በመጠየቅ እና በማበረታታት፣ በተለያየ ችግር ውስጥ የሚገኙት ወገኖቻችን በዓሉን በደስታ ማክበር ይችሉ ዘንድ ያለንን በማካፈል መሆን አለበት ሲል አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

በዓሉ ሲከበር ለሀገራችን ሰላም፣ ለሕዝባችን አንድነት እና በረከት ከልብ የሆነ ዱዓ በማድረግ መሆን አለበት ነው ያለዉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...