ከሪል ስቴት ሽያጭ ከ1.3 ትሪሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደሚገኝ ጥናት አሳይቷል

Date:

ይህ የተባለው  ጊፍት ሪል ስቴት ለሶስት ቀን የሚቆይ የ30 በመቶ ቅናሽ የአፓርትመንት የንግድ ሱቆች ሽያጭ ሲጀምር ነው፡፡

ሱቆቹን በ2 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ ለገዥዎች ለማስረከብ ተዘጋጅቻለሁ ብሏል፡፡

ድርጅቱ ተመራጭ የሆኑ ዲዛይኖችን እና አዳዲስ እሴቶችን በማካተት ከዚህ ቀደም በሲ ኤም ሲ አካባቢ በ 16,000 ካሬ ሜትር እና በ95,000 ካሬ ሜትር  ላይ ሁለት መንደሮችን ገንብቶ ለደንበኞቹ ማስተላለፉን ሰምተናል፡፡

በተያያዘም ፈረስ ቤት አካባቢ በ50,000 ካሬ ሜትር ላይ ሶስተኛውን መንደር ገንብቶ ለነዋሪዎች ማስረከቡንም ተናግሯል፡፡

በአሁኑ ደግሞ በአዲስ አበባ በለገሃር፣ በተክለሀይማኖት፣ በ22 ማዞሪያ፣ በፈረስ ቤት የመኖሪያና የንግድ አፓርታማ መንደሮችን እየገነባ እንደሚገኝና ለሽያጭ ማቅረቡንም ተናግሯል፡፡

በዚህም ከሚያዝያ 2 እስከ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ለሽያጭ ክፍት ነው ተብሏል፡፡ 

ከሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...