ከጢስ ዓባይ ቀጥሎ በኢትዮጵያ 2ኛው ትልቁ ፏፏቴ

Date:


የሶር ፏፏቴ በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦር ዞን በቾ ወረዳ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ ፏፏቴው ከኢሉ አባቦር ዞን መቱ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ የቱርስት መስህብ ቢሆንም መሰረተ ልማቶች ባለመሟላታቸው በጎብኝዎች ዘንድ ብዙም ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡

ሶር የተሰኘው ወንዝ የፏፏቴው መነሻ ሲሆን፤ ወንዙ የመቱን ከተማ አቋርጦ የሚያያልፍ ነው፡፡

በስፋቱም ሆነ በርዝመቱ ከጢስ ዓባይ ቀጥሎ ትልቅ እንደሆነ የሚነገርለት ሶር ፏፏቴ፤ ወቅቶች ሲፈራረቁ የፏፏቴው መጠን ከፍ እና ዝቅ እንደሚል ይነገራል፡፡

ይህ የተፈጥሮ መስህብ ትኩረት ተሰጥቶት መልማት ቢችል በቱሪዝም ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የድርሻውን ገቢ ማበርከት የሚችል የተፈጥሮ ሀብት መሆኑ ይገለፃል፡፡

ዙሪያውን በተፈጥሮ ቡና እና ጥቅጥቅ ባለ ደን የተከበበው ሶር ፏፏቴ፣ የቱሪስቶችን ቀልብ ለመግዛት የሚያስችል አስደናቂ መልክዓ ምድርንም የተላበሰ ነው፡፡

50 ሜትር ቁመት እና 78 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ፏፏቴው፤ ወደ ታች በሚንደረደርበት ወቅት ልክ እንደ ጢስ ዓባይ ለአካባቢው ልዩ ውበት እንደሚያላብሰው ይነገራል፡፡

የሶር ፏፏቴ ከአስደናቂ መልክዓ ምድሩ በተጨማሪ፤ እንደ ዝንጀሮ፣ ጉሬዛ እና ድኩላ ያሉ የዱር እንስሳትን አስጠልሎ ይገኛል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...