ከፈንታሌ ወረዳ ስድስት ሰዎች በኮሌራ በሽታ ህይወታቸው አለፈ

Date:

በኦሮሚያ ክልል በፈንታሌ ወረዳ በመሬት በተከሰተው መንቀጥቀጥ የተፈናቀሉ ስድስት ሰዎች በንፁህ ውሃ እጦት ምክንያት በተከሰተ የኮሌራ በሽታ መሞታቸውን የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ አሰቦት ለአዲስ ስታንዳርድ ተናገሩ።

ኃላፊው ተፈናቃዮቹ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በማጣታቸው የዝናብ ውሃን ለመጠጥነት እየተጠቀሙ መሆኑን በመግለጽ፤ “በርካታ ሰዎች በኮሌራ በሽታ ተይዘው ስድስት ሰዎች ሞተዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ፤ “ከዚህ ቀደም እርዳታ በቡሳ ጎኖፋ እና በእርዳታ ድርጅቶች በኩል ይሰጥ ነበር” ሲሉ ገልጸው፤ አሁን ግን ሲደረግልን የነበረው እርዳታ “ሙሉ ለሙሉ ተቋርጧል” ብለዋል።

በተመሳሳይ መልኩ በ አፋር ክልል እንደ ዱለቻ እና አዋሽ ፋንታሌ ካሉ ወረዳዎች ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች በእርዳታ እጦት እየተቸገሩ መሆኑን ለአዲስ ስታንዳርድ አስረድተዋል።

ከአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ መፈናቀላቸውን የተናገሩት መሀመድደወል ኦስማን፤ “የሰብዓዊ እርዳታ ቢያንስ ላለፉት ሶስት ወራት ተቋርጧል” ሲሉ ጠቅሰው፤ ተፈናቃዮቹ በምግብ እና የመጠጥ ውሃ እጦት ችግር ውስጥ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት አጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን...

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን በሀገር-በቀል አቅም ለማጠናከር የሚያስችል ግብረ ኃይል ተቋቋመ

የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሀገር ውስጥ አቅም ላይ...

ዶናልድ ትራምፕ የ’ICE’ ተቋምን ስም ወደ ‘NICE’ ለመቀየር መወሰናቸው አነጋጋሪ ሆነ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የኢሚግሬሽን እና የጉምሩክ አስከባሪ...

የአዲስ አፍሪካ ሪል እስቴት ኤክስፖ የአራት ቀናት ስኬታማ የሥራ ክንውን

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት አልሚዎች ማኅበር ባለቤትነት እንዲሁም በከተማ መሠረተ...