የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ብሔራዊ ኢንተርፖል፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን በጋራ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ከ338 ሚሊዮን ብር በላይ የዋጋ ግምት ያላቸው ሕገ-ወጥ መድኃኒቶች መያዛቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስዩም ወልዴ፤ በሕገ ወጥ የመድኃኒት ዝውውር ላይ ተሰማርተው ህብረተሰቡን ለከፋ የጤና ችግር እየዳረጉ ያሉ አካላትን በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተናግረዋል።
