
የፈረንሳዩ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናል ካናል ፕላስ በኢትዮጵያ ከታህሣሥ 22/04/2017 ዓ.ም ጀምሮ ስርጭቱን እንደሚያቋርጥ አስታወቀ። ካናል ፕላስ በማህበራዊ ትስስር ገፁ “የፕሮግራም ስርጭታችንን ታህሳስ 22 2017 ስለምናቋርጥ የደንበኝነት እድሳት እስከ ጥቅምት 21/2017 ድረስ ይቆያል” ብሏል። በተጨማሪም ቴሌቪዥን ጣቢያው “ለነበረንም ቆይታ በድጋሚ ከልብ እናመሰግናለን” በማለት ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ካናል ፕላስ እንደሚታወቀው በኢትዮጵያ ከስታር ታይምስ እና ዲ ኤስ ቲቪ ቀጥሎ ሶስተኛው የሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናል ነበር።