ክሪስታል ፓላስ የአውሮፓ ዋንጫ በማንሳት ታሪክ ሠራ

Date:

ትናንት ምሽት በኮንፍረንስ ሊግ ፍጻሜ የስፔኑን ራዮ ቫልካኖን 1-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በታሪካቸው የመጀመሪያውን የአውሮፓ ዋንጫ አነሱ።

ለብዙ ዓመታት በደረጃ ሰንጠረዥ ግርጌ ላል ከሊጉ ላለመውረድ ሲፋለሙ የቆዩት ፓላሶች በኦሊቨር ግላስነር መሪነት ፍጹም የተለየ ቡድን ሆኗል። በዚህ ውድድርም ፊዮረንቲናን እና ሻካታር ዶኔትስክ ያሉ ጠንካራ ቡድኖችን አሸንፈው ወደ ፍጻሜው ደርሰዋል።

በፍጻሜው ጨዋታ የድሉን ጎል ያስቆጠረው ጃን ፊሊፕ ማቴታ ነበር። ይህ ጎል የሰለረስት ፓርክ ደጋፊዎችን ወደ እብደት ደስታ አስገባ።

🗣️ ኦሊቨር ግላስነር “ይህ ለክለቡ እና ለደጋፊዎቹ የማይረሳ ሌሊት ነው” ብሎ ተናግሯል።

ማቴታም በበኩሉ “ይህን ዋንጫ ለደጋፊዎቻችን አሸንፈናል” ብሎ በደስታ ተናግሯል።

ክሪስታል ፓላስ አሁን ከወራጅ ቀጠና ቡድንነት ወደ ዩሮፕያን መድረክ የተሳካ ጉዞ ተቀይሯል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...