የ2017 ዓ.ም የዘመን ገበያ አዲስ አመት ኤግዚቢሽንና ባዛርን ለማዘጋጀት ታሜሶል ኮሚዩኒኬሽን በ92.8 ሚሊዮን ብር ጨረታ ማሸነፉ ተገልጿል ።
ይህ ትልቅ ዝግጅት “ዘመን ገበያ አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት ኤክስፖ 2018” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከነሐሴ 17 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በሽርክና የሚዘጋጅ ሲሆን፣ የቴሌብር ሱፐርአፕን ለህብረተሰቡ በስፋት ለማስተዋወቅ ታስቦበት እንደሆነም ታውቋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ300 በላይ የአገር ውስጥ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጪዎች የሚሳተፉ ሲሆን፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከቻይና፣ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ከሌሎች ሀገራት የመጡ ኤግዚቢተሮችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።
የኤግዚቢሽኑ ተሳታፊዎች ለህብረተሰቡ ሰፊ ምርጫ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ከትምህርት ቁሳቁስ፣ የቤት እቃዎች እና ቴክኖሎጂን ጨምሮ የተለያዩ የፍጆታ ዕቃዎች ይቀርባሉ ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ ዋና ዋና ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙበት ልዩ “ፋይናንስ መንደር” የሚል ቦታ መዘጋጀቱ በዝግጅቱ ላይ ተጨማሪ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
