የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን “ሕገወጥ የፖለቲካ ፓርቲ” ብሎ መሰረዙን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ለፀጥታ ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ስብሰባ ጥሪ አቀረበ።
ህብረቱ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ መውደቁን በመግለጽ፣ ሁኔታው ወደ ከፋ ግጭት ከማምራቱ በፊት በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈለግ አሳስቧል።
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሰብሳቢ ክቡር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ለምክር ቤቱ በላኩት ደብዳቤ፤ የኢብም ውሳኔ የሰላም ስምምነቱን በግልጽ የሚፃረርና በሰሜን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የተደረገውን ጥረት የሚያደናቅፍ ነው ብለዋል።
ህብረቱ፤ ምክር ቤቱ በአስቸኳይ በመሰብሰብ በጉዳዩ ላይ እንዲወያይና ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል።
