ይህ እንዳደርግም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በደንብ ቁጥር 185/2017 የተደነገገው ደንብ ይፈቅድልኛል ብሏል፡፡
በዚህ ደንብ መሠረት በከተማዋ ማንኛውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት የትራንስፖርት አገልግሎትን መስጠት እንደሚጠበቅበት ተደንግጓል ሲል ተናግሯል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከስምሪት መስመር ውጪ አገልግሎት መስጠት፣ አቆራርጦ መጫንና ቢሮው ካወጣው ታሪፍ ውጪ ተሳፋሪን ማስከፈል እንደማይቻል ቢሮው በብርቱ አሳስቧል፡፡
