“የሆርሙዝ ወሽመጥ የኢራን የማያሻማ ሉዓላዊ ግዛት አካል ነው” – የኢራን ጦር

Date:

ሆርሙዝ ወሽመጥ የማያሻማ የኢራን ሉዓላዊ የውሃ አካል በመሆኑ ለወራሪዎች ቦታ እንደሌለው ኻታም አል-አንቢያ በመባል የሚታወቀው የኢራን ጦር ሠራዊት ማዕከላዊ ማዘዣ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ስለዚህም “ከአሜሪካ በኩል በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የሚደረግ የትኛውም ዓይነት ጠልቃ ገብነት ከኢራን ጦር ኃይሎች ፈጣን እና የማያዳግም ምላሽ ይሰጠዋል” በማለት አስጠንቅቋል።

ከማዘዣ ማዕከሉ የወጣውን መግለጫ ጠቅሰው የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት “ወሳኝ የውሃ ላይ መተላለፊያ የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነት እና አስተዳደር ጉዳይ የኃያላኑ የእስላማዊት ኢራን ጦር ኃይሎች የማይታለፍ ቀይ መስመር ነው” በማለት አጽንኦት መስጠቱን አመልክተዋል።

“ሆርሙዝ ወሽመጥ የወራሪዋ አሜሪካ የምትቆጣጠረው መስክ ሳይሆን፣ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የማያሻማ ሉዓላዊ ግዛት ነው” ሲል ኢራን በባሕር መተላለፊያው ላይ ያላትን የበላይነት ገልጿል።

ሁሉም የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ደኅንነታቸው ተጠብቆ በሰላም ለማለፍ በኢራን የተቀመጠውን መስመር ብቻ መከተል እንዳለባቸው እና ካልሆነ ግን የሚገጥማቸውን ቅጣት መቀበል እንደሚገባቸው አስጠንቅቋል።

ኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል ጦርነት ከተከፈተባት በኋላ በወሳኙ የባሕር መስመር በኩል ላይ በሚያልፉ መርከቦች ላይ ጥቃት መሰንዘር በመጀመሯ ሆርሙዝ ዝግ ሆኖ ቆይቷል።

ሆርሙዝ ከዓለም ፍጆታ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆነው ነዳጅ እና ጋዝ ከፋርስ ባሕረ ሰላጤው አገራት በመነሳት የሚተላለፍበት ወሳኝ የባሕር መስመር ነው። በጦርነቱ ወቅት መርከቦች ማለፍ ባለመቻላቸው በዓለም ዙሪያ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቶ ነበር።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዜጋዬ ተገድሏል ያለችው ጋና ከደቡብ አፍሪካ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ውስጥ ገባች

አንድ ጋናዊ በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ካለው ፀረ ስደተኞች ተቃውሞ...

«የማይናገረው ልዑል» መጽሐፍ በታላቅ ድምቀት ሊመረቅ ነው

ደራሲ መሠረት ክንፈ ኃይሌ ከኦቲዝም ጋር ከሚኖረው ልጇ ልዑል...

በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር የሚደረግ ንግድ በገንዘብ መጠን ተገደበ

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር የሚከናወነውን...

(IMF) ከ460 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር አፀደቀ

አዳዲስ ብድር በመውሰድ ረገድ ጥንቃቄ እንድታደርግ ኢትዮጵያን ያስጠነቀቀው IMF...