የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን የፈንድ እጥረት ለመቀነስ እየተሰራ ነዉ

Date:

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን የገቢ ምንጭ ለማመንጨት የሶሻል ኢንተርፕራይዞች አማራጭ አድርጎ ለመጠቀም የፖሊሲ ክፍተት እንዳለ ተጠቁሟል።

በኢትዮጵያ የሶሻል ኢንተርፕራይዞችን የሚመራ የህግ ማዕቀፍ አለመኖሩ ተገልጿል።

ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን የፖሊሲ ጥናቱን እያስጠና ያለዉ የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ነዉ።

ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጡን የጠየቅናቸዉ የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የፕሮጀክት አስተዳደር አጋርነት ሀላፊ አቶ እድሪስ የሱፍ ናቸዉ።

አቶ እድሪስ እንደገለጹት፤ከፈንዶች መቋረጥ ጋር ተያይዞ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶቹ ሀገር በቀል ምንጮች እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ስለመገኘቱ ገልፀዋል።

‹‹የሶሻል ኢንተርፕራይዞች በዋናነት ቢዝነስ ቢሰሩም፤ ትርፉን አትርፈዉ ያገኙትን ትርፍ ለማህበረሰቡ እርዳታ የሚያዉሉበት አሰራር በሌላዉ አለም አለ ››ሲሉም አስረድተዋል።

ሆኖም በኢትዮጵያ እንደዚህ ያሉ ተቋማትን ለማገዝ አሁን ላይ ያሉ የማያመቹ ህጎች ቅሬታ የሚያስነሱም ናቸዉ።

አቶ እድሪስ የሱፍ ‹‹እኛ ሀገር ሶሻል ኢንተርፕራይዝ ሲባል ሀሳቡም አዲስ ይመስላል፤ ይሄን የሚገዛ ህግም የለም›› ብለዉናል።

ራሳቸዉን በዚህ ድርጅት ስር ያስቀመጡ ተቋማት ያላቸዉ ሚና ታዉቆ ከነጋዴ እኩል ከትርፋቸዉ የሚወሰደዉም ታክስ እንዲታይላቸዉ የሚያደርግ የህግ ማዕቀፍ ይዘጋጃል ተብሏል።

ሀላፊዉ እየተካሄደ ያለዉ ጥናት በበጎ አድራጎት እና በንግድ ትርፋቸዉ ላይ አሰራር ለማበጀት የሚያስችል ይሆናል ብለዋል።

እየተዘጋጀ ያለዉ የፖሊሲ ጥናት በስድስት ወራት ዉስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...